የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • wp17 ቁጥር 3 ገጽ 9
  • ተጨማሪ ማስረጃ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ተጨማሪ ማስረጃ
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2017
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • በአምላክ እርዳታ መተማመን
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • የዕዝራ መጽሐፍ ጎላ ያሉ ነጥቦች
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2006
  • ዕዝራ የመጽሐፉ ይዘት
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1. ታሪኮቹ ትክክል መሆናቸው
    ንቁ!—2007
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2017
wp17 ቁጥር 3 ገጽ 9
ታታኑ የሚለው ስም የተጻፈበት የኪዩኒፎርም ጽላት

በዚህ የኪዩኒፎርም ጽላት በአንደኛው ጎን ላይ “ታታኑ” የሚለው ስም ተጽፎ ይገኛል

ተጨማሪ ማስረጃ

የመጽሐፍ ቅዱስን ዘገባ የሚደግፉ አርኪኦሎጂያዊ ማስረጃዎች አሉ? ቢብሊካል አርኪኦሎጂ ሪቪው የተሰኘ አንድ መጽሔት በ2014 ይዞት የወጣው ርዕስ “በዕብራይስጥ ቅዱሳን መጻሕፍት ውስጥ ከተጠቀሱት ሰዎች መካከል አርኪኦሎጂያዊ ማስረጃ የተገኘላቸው ምን ያህሎቹ ናቸው?” ለሚለው ጥያቄ ማብራሪያ ሰጥቷል። መጽሔቱ “ቢያንስ 50” የሚሆኑት አርኪኦሎጂያዊ ማስረጃ እንደተገኘላቸው ገልጿል! በዚያ ርዕስ ላይ ካልተጠቀሱት ሰዎች መካከል አንዱ ታተናይ ነው። ታተናይ ማን ነው? በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለ እሱ ምን እንደተባለ እስቲ እንመልከት።

ኢየሩሳሌም በአንድ ወቅት የፋርስ ግዛት ክፍል ነበረች። ከተማዋ የምትገኘው ፋርሳውያን ‘ከወንዙ ባሻገር ያለው ክልል’ ብለው ይጠሩት በነበረው ከኤፍራጥስ በስተ ምዕራብ ባለው አካባቢ ነበር። ፋርሳውያን ባቢሎንን ድል ካደረጉ በኋላ በዚያ የሚገኙትን አይሁዳውያን ምርኮኞች በመልቀቅ በኢየሩሳሌም የይሖዋን ቤተ መቅደስ ዳግመኛ እንዲገነቡ ፈቀዱላቸው። (ዕዝራ 1:1-4) ይሁንና የአይሁዳውያን ጠላቶች የቤተ መቅደሱን ግንባታ ከመቃወማቸውም በላይ አይሁዳውያን ይህን የሚያደርጉት በፋርስ ላይ በማመፅ እንደሆነ የሚገልጽ ክስ ሰነዘሩባቸው። (ዕዝራ 4:4-16) በቀዳማዊ ዳርዮስ የግዛት ዘመን (522-486 ዓ.ዓ.) ታተናይ የተባለ የፋርስ ባለሥልጣን ይህን ለማጣራት ምርመራ አካሄደ። መጽሐፍ ቅዱስ ታተናይን “ከወንዙ ባሻገር ያለው ክልል ገዢ” በማለት ይጠራዋል።—ዕዝራ 5:3-7

ታተናይ የሚለውን ስም የያዙ በርካታ የኪዩኒፎርም ጽላቶች ተገኝተዋል፤ ጽላቶቹ የአንድ ቤተሰብን ታሪካዊ መረጃ የያዙ ሰነዶች ሳይሆኑ አይቀሩም። ከእነዚህ ጽላቶች አንዱ የዚህ ቤተሰብ አባል የሆነን አንድ ሰው ከታተናይ ጋር አያይዞ ይጠቅሳል፤ ጽላቱ በቀዳማዊ ዳርዮስ 20ኛ የግዛት ዘመን ማለትም በ502 ዓ.ዓ. የተጻፈን አንድ የክፍያ ውል የያዘ ነው። የውሉ ምሥክር “ከወንዙ ባሻገር ያለው ክልል ገዢ የሆነው የታታኑ” አገልጋይ እንደሆነ ጽላቱ ላይ ተገልጿል፤ እዚህ ላይ የተጠቀሰው ታታኑ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ባለው የዕዝራ መጽሐፍ ላይ የተጠቀሰው ታተናይ ነው።

ይህ ሰው ያለው ሥልጣን ምን ነበር? ታላቁ ቂሮስ በ535 ዓ.ዓ. ግዛቱን በአውራጃዎች ከፋፍሎ ነበር፤ ከእነዚህ አውራጃዎች አንዱ ባቢሎንና ከወንዙ ባሻገር ያለው ክልል በመባል ይጠራ ነበር። ከጊዜ በኋላ ይህ አውራጃ ለሁለት ተከፈለና አንዱ “ከወንዙ ባሻገር ያለው ክልል” ተብሎ መጠራት ጀመረ። ይህ ክልል ኮይሌ-ሶርያን፣ ፊንቄን፣ ሰማርያንና ይሁዳን ይጨምር ነበር፤ የዚህ ክልል ገዢ በደማስቆ ተቀምጦ ይገዛ የነበረ ይመስላል። ታተናይ ከ520 እስከ 502 ዓ.ዓ. ድረስ ይህን ክልል ገዝቷል።

ታተናይ ‘አይሁዳውያን ዓምፀዋል’ የሚለውን ክስ ለመመርመር ወደ ኢየሩሳሌም ከተጓዘ በኋላ አይሁዳውያኑ ‘የይሖዋን ቤተ መቅደስ መልሶ ለመገንባት ከቂሮስ ፈቃድ አግኝተናል’ እንዳሉ ለዳርዮስ ገለጸለት። ከዚያም በግምጃ ቤቱ ውስጥ የተደረገው ምርመራ አይሁዳውያኑ የተናገሩት ነገር ትክክል እንደሆነ አረጋገጠ። (ዕዝራ 5:6, 7, 11-13፤ 6:1-3) በመሆኑም ታተናይ በግንባታው ላይ ጣልቃ እንዳይገባ ታዘዘ፤ እሱም እንደታዘዘው አደረገ።—ዕዝራ 6:6, 7, 13

እርግጥ ነው፣ “ከወንዙ ባሻገር ያለው ክልል ገዢ የሆነው ታተናይ” በታሪክ ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ሰው አይደለም። ሆኖም መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስሙ እንደተጠቀሰና የተሰጠው ማዕረግም ትክክለኛ እንደሆነ ልብ በል። ይህ እውነታ የአርኪኦሎጂ ግኝቶች መጽሐፍ ቅዱስ ከታሪክ አኳያ ትክክል እንደሆነ እንደሚያረጋግጡ የሚያሳይ ተጨማሪ ማስረጃ ነው።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ