የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w17 ጥቅምት ገጽ 32
  • ይህን ያውቁ ኖሯል?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ይህን ያውቁ ኖሯል?
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2017
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የአንባቢያን ጥያቄዎች
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2022
  • የአንባብያን ጥያቄዎች
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2003
  • ቃላችሁ አዎ ከሆነ አዎ ይሁን
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2012
  • ከአንባቢዎቻችን
    ንቁ!—2009
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2017
w17 ጥቅምት ገጽ 32

ይህን ያውቁ ኖሯል?

ኢየሱስ መሐላን ያወገዘው በየትኛው የአይሁዳውያን ልማድ የተነሳ ነው?

አንድ ሰው በቤተ መቅደሱ ውስጥ መሐላ ሲፈጽም

በሙሴ ሕግ መሠረት፣ መማል ተገቢ የሚሆንባቸው ጊዜያት ነበሩ። በኢየሱስ ዘመን የነበሩ አይሁዳውያን ግን በትንሽ በትልቁ የመማል ልማድ ተጠናውቷቸው ነበር። እንዲህ የሚያደርጉት የተናገሩት ነገር ይበልጥ ተአማኒነት እንዲኖረው ለማድረግ ሲሉ ነበር፤ ሆኖም ኢየሱስ ከአንዴም ሁለት ጊዜ ይህን ልማድ አውግዞ ተናግሯል። ኢየሱስ “ቃላችሁ ‘አዎ’ ከሆነ አዎ ይሁን፤ ‘አይደለም’ ከሆነ አይደለም ይሁን” በማለት አስተምሯል።—ማቴ. 5:33-37፤ 23:16-22

ቲኦሎጂካል ዲክሽነሪ ኦቭ ዘ ኒው ቴስታመንት እንደገለጸው “አይሁዳውያን የሚናገሩትን ነገር ሁሉ በመሐላ የማረጋገጥ ልማድ” ምን ያህል ተጠናውቷቸው እንደነበር በታልሙድ ላይ ከሰፈረው ሐሳብ ማየት ይቻላል፤ ታልሙድ እንደ ጽኑ መሐላ የሚቆጠሩትንና የማይቆጠሩትን መሐላዎች አንድ በአንድ ይዘረዝራል።

እንዲህ ያለውን መሐላን ያላግባብ የመጠቀም ልማድ ያወገዘው ኢየሱስ ብቻ አልነበረም። ለምሳሌ ያህል፣ አይሁዳዊው ታሪክ ጸሐፊ ፍላቪየስ ጆሴፈስ አንድን የአይሁድ ኑፋቄ ቡድን አስመልክቶ እንዲህ ብሎ ነበር፦ “[የዚህ ኑፋቄ ቡድን አባላት] መሐላ መፈጸምን በሐሰት ከመመሥከር የከፋ እንደሆነ አድርገው ስለሚቆጥሩ ከመማል ይቆጠቡ ነበር። ምክንያቱም በአምላክ ስም ካልማለ በቀር ሊታመን የማይችል ሰው ቀድሞውኑም ቢሆን የተወገዘ ነው የሚል አመለካከት አላቸው።” በተጨማሪም የሲራክ ጥበብ ወይም ኤክሊዚያስቲከስ በመባል የሚታወቀው የአይሁዳውያን አዋልድ ጽሑፍ (23:11) “መማል የሚወድ ሰው የለየለት ሕገ ወጥ ሰው ነው” በማለት ይናገራል። ከዚህ ማየት እንደሚቻለው፣ ኢየሱስ ያወገዘው በረባ ባልረባው የመማል ልማድን ነው። አንድ ሰው ሁልጊዜ እውነቱን የሚናገር ከሆነ የሚናገረው ነገር ይበልጥ ተአማኒነት እንዲኖረው ለማድረግ ሲል መማል አያስፈልገውም።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ