የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 11/07 ገጽ 3
  • የጥያቄ ሣጥን

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የጥያቄ ሣጥን
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2007
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ‘ከንቱ ነገርን’ ከመከታተል ተጠበቁ
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2002
  • በኢንተርኔት እንዳትጭበረበር ተጠንቀቅ!
    ንቁ!—2012
  • እባካችሁ ወዲያውኑ ሄዳችሁ አነጋግሯቸው
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2003
  • የናሙና ደብዳቤ
    ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ—2019
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—2007
km 11/07 ገጽ 3

የጥያቄ ሣጥን

◼ የግላችንን የኢሜይል አድራሻ በምናሰራጫቸው ጽሑፎች ላይ መለጠፋችን ተገቢ ነው?

አንዳንድ አስፋፊዎች የራሳቸውን የኢሜይል አድራሻ በማኅተም በማስቀረጽ ለሰዎች በሚያበረክቷቸው መጽሔቶችና ትራክቶች ላይ ያትማሉ ወይም በወረቀት አዘጋጅተው በጽሑፎቹ ላይ ይለጥፋሉ። ይህም ጽሑፉን የተቀበሉት ሰዎች ተጨማሪ መረጃ በሚፈልጉበት ጊዜ አስፋፊውን በቀላሉ ለማግኘት ያስችላቸዋል። ፍላጎት ያሳዩትን ለመርዳት የሚደረጉት እነዚህ ጥረቶች በቅን ልቦና የሚደረጉ ናቸው። ነገር ግን የይሖዋ ምሥክሮች ድረ ገጽ በመጽሔቶችና በትራክቶች ጀርባ ላይ ይገኛል። በመሆኑም የግል የኢሜይል አድራሻችንን በምናበረክታቸው ጽሑፎች ላይ ባንለጥፍ የተሻለ ነው።

አንድ አስፋፊ በክልሉ ውስጥ ለሚገኙ ሰዎች በተለይ ተመላልሶ መጠየቅ በሚያደርግበት ጊዜ የሚገኝበትን አድራሻ በወረቀት ላይ ጽፎ መስጠት አለመስጠት የግሉ ውሳኔ ነው። ጽሑፍ ያበረከትንላቸው ሰዎች ተጨማሪ መረጃ ሲፈልጉ እነሱ እስኪያነጋግሩን ድረስ ከመጠበቅ ይልቅ ፍላጎት ያሳዩትን ተመልሰን ለመጠየቅ እኛው ራሳችን ቅድሚያውን መውሰድ ይገባናል። ግለሰቡ ፍላጎት ያለው መሆን አለመሆኑን ይበልጥ ማወቅ የምንችለው ፊት ለፊት በምንነጋገርበት ጊዜ ነው።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ