የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 12/08 ገጽ 10
  • መጽሔቶችን ለማበርከት ምን ማለት ይቻላል?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • መጽሔቶችን ለማበርከት ምን ማለት ይቻላል?
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2008
  • ንዑስ ርዕሶች
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ንቁ! ታኅሣሥ 2008
  • መጽሔቶችን ለማበርከት ምን ማለት ይቻላል?
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2006
  • መጽሔቶችን ለማበርከት ምን ማለት ይቻላል?
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2007
  • መጽሔቶችን ለማበርከት ምን ማለት ይቻላል?
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2001
  • መጽሔቶችን ለማበርከት ምን ማለት ይቻላል?
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2004
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—2008
km 12/08 ገጽ 10

መጽሔቶችን ለማበርከት ምን ማለት ይቻላል?

መጠበቂያ ግንብ ኅዳር 1

“ብዙ ሰዎች፣ አምላክ አፍቃሪ ነው ብለው ቢያምኑም ሰዎችን ለዘላለም እንደሚያሠቃይ የሚናገረው ትምህርት ግራ ያጋባቸዋል። እርስዎስ ስለዚህ ጉዳይ ምን አመለካከት አለዎት? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] መጽሐፍ ቅዱስ፣ አምላክ ክፉ ወይም ቂመኛ እንዳልሆነ ያስተምራል። [ሕዝቅኤል 18:23ን አንብብ።] ይህ መጽሔት ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ትኩረት የሚስቡ ቅዱስ ጽሑፋዊ ማስረጃዎችን ይዟል።”

ንቁ! ኅዳር 2008

“በዓለም ዙሪያ የሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ወደ አምላክ ይጸልያሉ። እኛም እንዲህ እንድናደርግ ግብዣ ቀርቦልናል። [1 ጴጥሮስ 5:7ን አንብብ።] ሆኖም በሕይወት ውስጥ በሚያጋጥሙት ጫናዎች የተነሳ ቅን የሆኑ በርካታ ሰዎች እንኳ ጸሎታቸው አጭርና በዘልማድ የሚቀርብ እንደሆነ ይሰማቸዋል። በመሆኑም እያንዳንዳችን ‘የጸሎቴን ይዘት ማሻሻል የምችለው እንዴት ነው?’ የሚለውን ጥያቄ ማንሳታችን አስፈላጊ ነው። [ገጽ 26ን አሳየው።] ይህ ርዕስ፣ የአምልኮታችን ዋነኛ ክፍል ከሆነው ከጸሎት ጋር በተያያዘ ልናሻሽላቸው የምንችላቸውን አንዳንድ ጠቃሚ ሐሳቦች ይዟል።”

መጠበቂያ ግንብ ታኅሣሥ 1

“በዚህ ወቅት ብዙ ሰዎች ስለ ኢየሱስ ያስባሉ። ኢየሱስ በሕይወትዎ ላይ ምን ተጽዕኖ አሳድሯል? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] መጽሐፍ ቅዱስ የኢየሱስን ፈለግ እንድንከተል ያበረታታናል። [1 ጴጥሮስ 2:21ን አንብብ።] እንዲህ ማድረጋችን ደግሞ ደስተኛና ጥሩ ሰዎች እንድንሆን ያስችለናል። ይህ መጽሔት የዚህን ምክንያት ያብራራል።”

ንቁ! ታኅሣሥ 2008

“ሰዎች ይህን ጥያቄ ለዘመናት ሲጠይቁ ኖረዋል። [በሽፋኑ ላይ ያለውን ጥያቄ አሳየው።] ለዚህ ጥያቄ አጥጋቢ መልስ ማግኘት የምንችለው ከየት ይመስልዎታል? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] መልሱን ለማግኘት ወደ አምላክ ዞር ማለት ያለብን ለምን እንደሆነ ልብ ይበሉ። [መዝሙር 100:3ን አንብብ።] መጽሐፍ ቅዱስ በዚህ ጉዳይ ላይ ምን እንደሚል ይህ መጽሔት ያብራራል።”

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ