የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 10/09 ገጽ 3
  • የጥያቄ ሣጥን

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የጥያቄ ሣጥን
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2009
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ‘ለምሥራቹ መሟገትና በሕግ የጸና እንዲሆን ማድረግ’
    ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ—2023
  • በአፓርታማዎች ውስጥ ‘በሚገባ መመሥከር’
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2008
  • እባካችሁ ወዲያውኑ ሄዳችሁ አነጋግሯቸው
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2003
  • የፖሊስ ጥበቃ—የሚያሳድረው ተስፋና የሚፈጥረው ሥጋት
    ንቁ!—2002
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—2009
km 10/09 ገጽ 3

የጥያቄ ሣጥን

◼ መስበካችሁን እንድታቆሙ ብትታዘዙ ምን ማድረግ ይኖርባችኋል?

አስፋፊዎች በአንድ ዓይነት የአገልግሎት መስክ እየተካፈሉ ሳለ ፖሊሶች መጥተው አስፋፊዎቹ ሕግ እንደጣሱ በመግለጽ መስበካቸውን እንዲያቆሙ የሚያዙበት ጊዜ አለ። እንዲህ ያለ ሁኔታ ካጋጠማችሁ አክብሮት በተሞላበት መንገድ ወዲያውኑ ክልሉን ለቃችሁ መውጣት ይኖርባችኋል። (ማቴ. 5:41፤ ፊልጵ. 4:5) ሕጋዊ መብት እንዳለን በመግለጽ ችግሩን በራሳችሁ ለመፍታት አትሞክሩ። የሚቻል ከሆነ የፖሊሱን መለያ ቁጥርና የተሠማራበትን አካባቢ (ወይም ቁጥሩን) በዘዴ ለመያዝ ጥረት አድርጉ። ከዚያም ወዲያውኑ ሁኔታውን ለሽማግሌዎች አሳውቁ፤ እነሱ የተፈጠረውን ሁኔታ ለቅርንጫፍ ቢሮው ሪፖርት ያደርጋሉ። በተመሳሳይም በአፓርታማ ውስጥ እያገለገላችሁ እያለ የጥበቃ ሠራተኞች ወይም ሌላ ማንኛውም የአፓርታማው ተወካይ ሕንፃውን ለቅቃችሁ እንድትወጡ ቢጠይቋችሁ ወዲያውኑ የተባላችሁትን ማድረግ ይኖርባችኋል፤ ከዚያ በኋላ ግን ሁኔታውን ለሽማግሌዎች አሳውቁ። ሥልጣን ያላቸውን ሰዎች በገርነትና በትሕትና መንፈስ መያዛችን አላስፈላጊ ችግር እንዳይፈጠር ሊረዳ ይችላል።—ምሳሌ 15:1፤ ሮም 12:18

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ