የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 10/11 ገጽ 8
  • የአቀራረብ ናሙናዎች

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የአቀራረብ ናሙናዎች
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2011
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የአቀራረብ ናሙናዎች
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2012
  • የአቀራረብ ናሙናዎች
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2014
  • መጽሔቶችን ለማበርከት ምን ማለት ይቻላል?
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2009
  • የአቀራረብ ናሙናዎች
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2012
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—2011
km 10/11 ገጽ 8

የአቀራረብ ናሙናዎች

በወሩ የመጀመሪያ ቅዳሜ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ለማስጀመር የሚረዳ አቀራረብ

“አምላክን ለመታዘዝ ጥረት የሚያደርጉ ሰዎች ደስተኞች እንደሆኑ ይሰማዎታል? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] እዚህ ርዕስ ላይ ጥሩ ሐሳቦችን ያገኛሉ።” ከዚያም የኅዳር 1⁠ን መጠበቂያ ግንብ ስጠውና በገጽ 16 እና 17 ላይ ካሉት ንዑስ ርዕሶች መካከል አንዱን መርጣችሁ ተወያዩበት። በተጨማሪም በንዑስ ርዕሱ ውስጥ ከሚገኙት ጥቅሶች መካከል ቢያንስ አንዱን አንብቡ። መጽሔቶቹን ካበረከትክለት በኋላ ከቀሪዎቹ ጥያቄዎች መካከል በአንዱ ላይ ለመወያየት ቀጠሮ ያዝ።

ኅዳር 1 መጠበቂያ ግንብ

“አንዳንዶች ከፆታ ሥነ ምግባር ጋር በተያያዘ መጽሐፍ ቅዱስ የሚሰጠው ሐሳብ ጊዜ ያለፈበትና የማያፈናፍን እንደሆነ ይሰማቸዋል። ሌሎች ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስ ከሚሰጠው መመሪያ ጋር ይስማማሉ። እርስዎስ ምን ይሰማዎታል? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] ሁለተኛ ጢሞቴዎስ 3:16 ላይ የሚገኘው ሐሳብ የመጽሐፍ ቅዱስ መሥፈርቶች ምንጭ ማን እንደሆነ ይናገራል። [ጥቅሱን አንብብ።] ስለ ፆታ ግንኙነት ለሚነሱ አሥር ጥያቄዎች መጽሐፍ ቅዱስ የሚሰጠው መልስ እዚህ መጽሔት ላይ ይገኛል። ከዚህም በተጨማሪ የመጽሐፍ ቅዱስ መሥፈርቶችን መከተል የሚጠቅመን እንዴት እንደሆነ ያብራራል።”

ኅዳር ንቁ!

“በዙሪያችን ያለውን አጽናፈ ዓለም ቆም ብለን ስንመለከት ምን ዓይነት መደምደሚያ ላይ የምንደርስ ይመስልዎታል? ፈጣሪ መኖሩን ወይስ ሁሉም ነገር የመጣው በአጋጣሚ መሆኑን? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ጸሐፊ አጽናፈ ዓለምን ከተመለከተ በኋላ የደረሰበትን መደምደሚያ አብረን እንመልከት። [ሮም 1:20⁠ን አንብብ።] ይህ መጽሔት የሳይንስ ሊቃውንት ስለ ሰው ልጆች ሴል የደረሱበትን ነገርና ይህ ደግሞ በአመለካከታችን ላይ የሚያመጣውን ለውጥ ያብራራል።”

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ