የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 6/12 ገጽ 4
  • የአቀራረብ ናሙናዎች

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የአቀራረብ ናሙናዎች
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2012
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የአቀራረብ ናሙናዎች
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2011
  • የአቀራረብ ናሙናዎች
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2014
  • የአቀራረብ ናሙናዎች
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2013
  • የናሙና አቀራረቦች
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2011
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—2012
km 6/12 ገጽ 4

የአቀራረብ ናሙናዎች

በወሩ የመጀመሪያ ቅዳሜ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ለማስጀመር የሚረዳ አቀራረብ

“ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ሰዎች ስለ መላእክት ለማወቅ ያላቸው ፍላጎት እየጨመረ መጥቷል። መላእክት በእርግጥ አሉ ብለው ያምናሉ? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] ስለዚህ ጉዳይ ይህ መጽሔት ምን እንደሚል ልብ ይበሉ።” የሐምሌ 1⁠ን መጠበቂያ ግንብ ስጠውና በገጽ 16 ላይ በሚገኘው በመጀመሪያው ንዑስ ርዕስ ሥር ያለውን ሐሳብ ተወያዩበት፤ በተጨማሪም እዚያ ላይ ከተጠቀሱት ጥቅሶች መካከል ቢያንስ አንዱን አብራችሁ አንብቡ። ከዚያም መጽሔቶቹን አበርክትለትና በቀጣዩ ጥያቄ ላይ ለመወያየት ቀጠሮ ያዝ።

ሐምሌ 1

መዝሙር 65:2⁠ን አንብብ። ከዚያም እንዲህ በል፦ “ብዙዎች እዚህ ላይ እንደተጠቀሰው አምላክ ጸሎትን እንደሚሰማ ስለሚያምኑ በየቀኑ ይጸልያሉ። አንዳንድ ሰዎች ግን ‘በእርግጥ አምላክ ካለ፣ በዓለም ላይ ይህ ሁሉ ችግር እንዴት ሊኖር ቻለ?’ ብለው ይጠይቃሉ። እርስዎ ስለዚህ ጉዳይ ምን ይላሉ? ጸሎታችንን የሚሰማ አምላክ አለ ብለው ያምናሉ? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] ይህ መጽሔት ‘ጸሎትን የሚሰማው አምላክ መከራ እንዲኖር የፈቀደው ለምንድን ነው?’ ለሚለው ጥያቄ ከመጽሐፍ ቅዱስ ላይ መልስ ይሰጣል።

ሐምሌ

“አቅም ቢኖርዎት ኖሮ በዓለም ላይ ካሉት ችግሮች መካከል የትኛውን ያስወግዱ ነበር? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] መጽሐፍ ቅዱስ የሰው ልጆች አቅም ውስን የሆነበትን ምክንያት ይገልጻል። [ኤርምያስ 10:23⁠ን አንብብ።] ይህ መጽሔት አምላክ ወደፊት ስለሚለውጣቸው ነገሮች ያብራራል።”

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ