የአቀራረብ ናሙናዎች
በወሩ የመጀመሪያ ቅዳሜ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ለማስጀመር የሚረዳ አቀራረብ
“ብዙዎች ‘አባታችን ሆይ’ የሚለውን ጸሎት ይጸልያሉ፤ በዚህ ጸሎት ላይ ‘መንግሥትህ ትምጣ፤ ፈቃድህ በሰማይ እንደ ሆነች፣ እንዲሁም በምድር ትሁን’ የሚል ሐሳብ ይገኛል። ስለዚህ መንግሥት ምንነት የሚያውቁት ነገር አለ? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] ይህን በተመለከተ ፍንጭ የሚሰጠን አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ አለ።” ዳንኤል 2:44ን አንብብ። ከዚያም የሐምሌ 1ን መጠበቂያ ግንብ ስጠውና ገጽ 16 ላይ በሚገኘው የመጀመሪያው ንዑስ ርዕስ ሥር ያለውን ሐሳብ አብራችሁ ካነበባችሁት በኋላ ተወያዩበት። መጽሔቱን እንዲወስደው ከጋበዝከው በኋላ በሌላ ጊዜ ተገናኝታችሁ በቀጣዩ ጥያቄ ላይ ለመወያየት ቀጠሮ ያዙ።
መጠበቂያ ግንብ ሐምሌ 1
“ሕይወት አጭርና በመከራ የተሞላ በመሆኑ ብዙዎች የሕይወትን ዓላማ በተመለከተ ግራ ተጋብተዋል። እርስዎስ ስለዚህ ጉዳይ አስበው ያውቃሉ? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] መጽሐፍ ቅዱስ ሕይወት በዚህ መልኩ እንደማይቀጥል ተስፋ ይሰጠናል። [ራእይ 21:4ን አንብብ።] ይህ መጽሔት አምላክ ለምድር ስላለው ዓላማ ያብራራል፤ እንዲሁም በአሁኑ ጊዜም እንኳ ትርጉም ያለው ሕይወት ለመምራት ምን ማድረግ እንደምንችል አንዳንድ ሐሳቦችን ይሰጣል።”
ንቁ! ሐምሌ
በዜና የሰማኸውን አንድ አሳዛኝ ሁኔታ ጥቀስ። ከዚያም እንዲህ በል፦ “አምላክ እንዲህ ያሉ ነገሮች እንዲከሰቱ የፈቀደው ለምን ይመስልዎታል? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] አምላክ መከራ ለሚደርስባቸው ሰዎች እንደሚያዝን መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል። [ዘፀአት 3:7ን አንብብ።] በተጨማሪም መጽሐፍ ቅዱስ አምላክ መከራ እንዲኖር የፈቀደበትን ምክንያትና በቅርቡ መከራን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንደሚያስወግድ ይገልጻል። ይህ መጽሔት ስለዚህ ጉዳይ ጥሩ ማብራሪያ ይዟል።”