የአቀራረብ ናሙናዎች
ለመታሰቢያው በዓል መጋበዣ የሚሆን የመግቢያ ሐሳብ
“መጋቢት 17, 2005 (እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር መጋቢት 26, 2013) በዓለም ዙሪያ በሚከበር ዓመታዊ የመታሰቢያ በዓል ላይ ከቤተሰብዎ ጋር እንዲገኙ የመጋበዣ ወረቀት ብሰጥዎ ደስ ይለኛል። ይህ ቀን ኢየሱስ የሞተበት ዕለት ነው። ከኢየሱስ ሞት ጥቅም ማግኘት የምንችለው እንዴት እንደሆነ የሚያብራራ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተመሠረተ ንግግር ይቀርባል፤ ይህ የመጋበዣ ወረቀት ስብሰባው በአካባቢያችን የሚደረገው የትና በስንት ሰዓት እንደሆነ ይገልጻል።”
መጠበቂያ ግንብ መጋቢት 1
“አንዳንድ ሰዎች ‘ኢየሱስ ከሞት መነሳቱን በእርግጠኝነት ማወቅ የምንችለው እንዴት ነው?’ በማለት ይጠይቃሉ። እርስዎ ስለዚህ ጉዳይ አስበው ያውቃሉ? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] ለዚህ ጥያቄ መልስ ማግኘት አስፈላጊ መሆኑን የሚያሳይ አንድ ጥቅስ ከመጽሐፍ ቅዱስ ላሳይዎት። [1 ቆሮንቶስ 15:14ን አንብብ።] ይህ መጽሔት የኢየሱስ ትንሣኤ የፈጠራ ታሪክ አይደለም የምንለው ለምን እንደሆነ ያብራራል።”
ንቁ! መጋቢት
“በአሁኑ ጊዜ ልጆችን ማሳደግ ከባድ እየሆነ መጥቷል ቢባሉ አይስማሙም? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] በርካታ ወላጆች ከመጽሐፍ ቅዱስ ግሩም ምክር አግኝተዋል። ለምሳሌ በቆላስይስ 3:21 [ጥቅሱን አንብብ።] ላይ የሚገኘው ጥቅስ አባቶች ልጆቻቸውን ለማመስገን የሚያስችሏቸውን አጋጣሚዎች በመፈለግ በራስ የመተማመን ስሜታቸውን ሊያሳድጉላቸው እንደሚችሉ ይናገራል። ይህ ርዕስ አባቶችን ሊረዱ የሚችሉ አምስት ምክሮችን ይዟል።”