የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 4/15 ገጽ 4
  • ቀጥተኛ ግብዣ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ቀጥተኛ ግብዣ
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2015
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ልዩ ግብዣ
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2014
  • ውጤት የሚያስገኝ ዘመቻ
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2013
  • ሰዎች በክልል ስብሰባ ላይ እንዲገኙ የምንጋብዝበት ዘመቻ
    ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ (2016)
  • የመታሰቢያው በዓል የመጋበዣ ወረቀት ሚያዝያ 2 መሰራጨት ይጀምራል
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2011
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—2015
km 4/15 ገጽ 4

ቀጥተኛ ግብዣ

1. ሰዎች በክልል ስብሰባ ላይ እንዲገኙ የመጋበዙ ዘመቻ የሚጀምረው መቼ ነው?

1 ለጓደኞቻችሁ ወይም ለቤተሰቦቻችሁ ብዙ ጉልበትና ወጪ የሚጠይቅ ልዩ የምግብ ግብዣ ለማድረግ ብታስቡ ግብዣው ላይ እንዲገኙ የምትጠሯቸው በደስታ ስሜት እንደሚሆን ምንም ጥያቄ የለውም። በተመሳሳይም በቅርቡ በምናካሂደው የክልል ስብሰባ ላይ የሚቀርበውን መንፈሳዊ ድግስ ለማዘጋጀት ብዙ ጥረት ሲደረግ ቆይቷል። ይሖዋ፣ ስብሰባው ከመጀመሩ ከሦስት ሳምንት ቀደም ብለን ሰዎች በዚህ ስብሰባ ላይ እንዲገኙ የመጋበዝ መብት ሰጥቶናል። ታዲያ ግብዣውን በደስታ ስሜት ማቅረብ እንድንችል ምን ይረዳናል?

2. በዘመቻው ላይ ሙሉ ተሳትፎ ለማድረግ የሚያነሳሳን ምንድን ነው?

2 ይሖዋ በክልል ስብሰባዎች አማካኝነት የሚሰጠን መመሪያ በግለሰብ ደረጃ ምን ያህል እንደሚጠቅመን የምናሰላስል ከሆነ በዘመቻው ላይ ሙሉ ተሳትፎ ለማድረግ እንነሳሳለን። (ኢሳ. 65:13, 14) በተጨማሪም በየዓመቱ የምናደርገው ይህ ዘመቻ ውጤት እንዳለው ማስታወስ ይኖርብናል። (“ውጤት ያስገኛል” የሚለውን ሣጥን ተመልከት።) ከምንጋብዛቸው ሰዎች መካከል ሁሉም ባይመጡም አንዳንዶቹ ስብሰባው ላይ ይገኛሉ። ግብዣውን ተቀብለው የሚመጡት ሰዎች ቁጥር ብዙም ይሁን ጥቂት የመጋበዣ ወረቀቱን ለማሰራጨት ከልብ ጥረት ማድረጋችን ለይሖዋ ክብር የሚያመጣ ከመሆኑም ሌላ የእሱን ለጋስነት ያሳያል።—መዝ. 145:3, 7፤ ራእይ 22:17

3. የመጋበዣ ወረቀቱን ማሰራጨት የሚቻለው እንዴት ነው?

3 የእያንዳንዱ ጉባኤ የሽማግሌዎች አካል፣ የመጋበዣ ወረቀቱን በጉባኤው ክልል ውስጥ ለብዙ ሰዎች ማዳረስ ስለሚቻልበት መንገድ ተነጋግሮ መወሰን አለበት፤ ይህም ቤታቸው ላልተገኙ ሰዎች የመጋበዣ ወረቀቱን ትቶ መሄድ ወይም የመጋበዣ ወረቀቱን በአደባባይ ምሥክርነት ማሰራጨት ያስፈልግ እንደሆነና እንዳልሆነ መወሰንን ይጨምራል። ቅዳሜና እሁድ፣ ሁኔታው አመቺ እንደሆነ ከተሰማን መጽሔቶችንም ማበርከት እንችላለን። በዚህ ሥራ በደስታ ስሜት የምንካፈልና ይሖዋ በሚያቀርበው መንፈሳዊ ድግስ ላይ በተቻለ መጠን ብዙ ሰዎች እንዲገኙ የምንጋብዝ ከሆነ ዘመቻው ሲጠናቀቅ ከፍተኛ እርካታ እንደምናገኝ የታወቀ ነው!

ምን ማለት ትችላላችሁ?

በአካባቢው የተለመደውን ሰላምታ ከሰጣችሁ በኋላ እንዲህ ማለት ትችላላችሁ፦ “በጣም አስፈላጊ በሆነ አንድ ዝግጅት ላይ እንዲገኙ በዓለም ዙሪያ ሰዎችን እየጋበዝን ነበር። ዝግጅቱ የሚካሄድበት ቀን፣ ሰዓትና ቦታ በዚህ የመጋበዣ ወረቀት ላይ ይገኛል።”

ውጤት ያስገኛል

  • ከተወሰኑ ዓመታት በፊት አንዲት እህት የመጋበዣ ወረቀት በማሰራጨቱ ዘመቻ ስትካፈል ይህ ሁሉ ጥረት መደረጉ ውጤት የሚያስገኝ ስለመሆኑ ጥርጣሬ ነበራት። ‘እውነት ሰዎች ጥሩ ምላሽ በመስጠት በስብሰባው ላይ ይገኛሉ?’ ብላ ታስብ ነበር። ቅዳሜ ዕለት በተካሄደው ስብሰባ ላይ አንድ የሲክ እምነት ተከታይ በአቅራቢያዋ ተቀምጦ ስላየች ቀረብ ብላ ተዋወቀችው። ከዚያ ሰውየው ወደ ስብሰባው የመጣው የመጋበዣው ወረቀት ደርሶት እንደሆነ ተገነዘበች። እህት ሰውየው ለነበሩት በርካታ ጥያቄዎች መልስ ሰጠችው። ግለሰቡ ስብሰባውን ምን ያህል እንደወደደውና በተሰብሳቢዎቹ አለባበስና ምግባር መደነቁን ነገራት። በዚያው ቀን ጥቂት ቆየት ብሎ እህት አጠገቧ ከተቀመጡ አንድ ባልና ሚስት ጋር ጨዋታ ጀመረች። እነሱም የተገኙት መጋበዣው ደርሷቸው ሲሆን ወደ ስብሰባው የመጡት አውቶብስ ተሳፍረው ነበር። ስብሰባውን በጣም ስለወደዱት እሁድም ለመምጣት እንዳሰቡ ተረዳች። በዚህ ጊዜ እህት በየዓመቱ የምናደርገው ዘመቻ ምን ያህል ውጤት እንዳለው ተገነዘበች።

  • በቅርቡ በተደረገ የክልል ስብሰባ ላይ የዘወትር አቅኚ የሆኑ አንድ ባልና ሚስት በዕድሜ ከገፉ ባልና ሚስት ጋር ተዋወቁ። ባልና ሚስቱ እዚህ ቦታ የተገኙት ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሆነ ተናገሩ። አቅኚዎቹም “ማን ነው የጋበዛችሁ?” ብለው ጠየቋቸው። እነሱም “አንድ ቀን ወደ ቤታችን ስንገባ የመጋበዣ ወረቀቱን በራችን ሥር አገኘን” በማለት መለሱ። ባልና ሚስቱ መጋበዣውን ያነበቡት ከመሆኑም በላይ ከጀርባ ያለውን ቅጽ ሞልተው ልከዋል። ሌሎች ወንድሞች ደግሞ ለባልና ሚስቱ ከያዙት ምሳ ላይ አካፈሏቸው። ስብሰባውን በጣም ስለወደዱት በሚቀጥለውም ቀን ለመምጣት ወሰኑ። ከዚያም ተከታትሎ የሚረዳቸው ሰው ተመደበላቸው።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ