የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • mwb18 የካቲት ገጽ 4
  • “አባትህንና እናትህን አክብር”

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • “አባትህንና እናትህን አክብር”
  • ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ—2018
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ሁሉንም ዓይነት ሰዎች ማክበር
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1991
  • አረጋውያን ወላጆቻችንን ማክበር
    ለቤተሰብ ደስታ ቁልፉ ምንድን ነው?
  • “አባትህንና እናትህን አክብር” ሲባል ምን ማለት ነው?
    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
  • ይሖዋን ማክበር—ለምንና እንዴት?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1991
ለተጨማሪ መረጃ
ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ—2018
mwb18 የካቲት ገጽ 4

ክርስቲያናዊ ሕይወት

“አባትህንና እናትህን አክብር”

ኢየሱስ ምድር ላይ በነበረበት ወቅት “አባትህንና እናትህን አክብር” የሚለውን ትእዛዝ የመጠበቅን አስፈላጊነት አጉልቶ ተናግሯል። (ዘፀ 20:12፤ ማቴ 15:4) ኢየሱስ እንዲህ ብሎ ለመናገር ነፃነት እንደሚሰማው እርግጠኞች መሆን እንችላለን፤ ምክንያቱም ልጅ ሳለ ወላጆቹን “ይታዘዛቸው” ነበር። (ሉቃስ 2:51 ግርጌ) አዋቂ ከሆነ በኋላም ለእናቱ አሳቢነት አሳይቷል፤ እሱ ከሞተ በኋላ እናቱን የሚንከባከብ ሰው እንዲኖር ዝግጅት አድርጓል።—ዮሐ 19:26, 27

በዛሬው ጊዜ ያሉ ክርስቲያን ልጆችም ለወላጆቻቸው በመታዘዝና እነሱን በአክብሮት በማነጋገር ወላጆቻቸውን እንደሚያከብሩ ያሳያሉ። ደግሞም ወላጆቻችንን እንድናከብር የተሰጠን ትእዛዝ የጊዜ ገደብ የለውም። ወላጆቻችን በዕድሜ ከገፉ በኋላም እንኳ፣ የሚሰጡንን ጥበብ ያዘለ ምክር በመስማት ለእነሱ አክብሮት ማሳየታችንን መቀጠል ይኖርብናል። (ምሳሌ 23:22) በተጨማሪም እንደ አስፈላጊነቱ ስሜታዊና ቁሳዊ ድጋፍ በማድረግ በዕድሜ የገፉ ወላጆቻችንን እንደምናከብር ማሳየት እንችላለን። (1ጢሞ 5:8) ልጆችም ሆን አዋቂዎች ወላጆቻችንን እንደምናከብር የምናሳይበት ዋነኛው መንገድ ከእነሱ ጋር ጥሩ የሐሳብ ግንኙነት እንዲኖረን በማድረግ ነው።

ወላጆቼን ማነጋገር የምችለው እንዴት ነው? የሚለውን የነጭ ሰሌዳ አኒሜሽን ቪዲዮ ተመልከት፤ ከዚያም የሚከተሉትን ጥያቄዎች ለመመለስ ሞክር፦

  • ወላጆችህን ማነጋገር የሚከብድህ ለምን ሊሆን ይችላል?

  • ወላጆችህን ስታነጋግር ለእነሱ አክብሮት እንዳለህ ማሳየት የምትችለው እንዴት ነው?

    አንድ ልጅ ለወላጆቹ ደብዳቤ ሲጽፍ፣ ከወላጆቹ ጋር ሲነጋገርና ከአባቱ ጋር ኳስ ሲጫወት
  • ወላጆችህን ለማነጋገር ጥረት ማድረግህ የሚክስህ እንዴት ነው? (ምሳሌ 15:22)

    ወላጆች ልጃቸው ወደፊት የሚጠብቁትን ተፈታታኝ ሁኔታዎች እንዲወጣ ሲያዘጋጁት

    ወላጆችህን ማነጋገርህ በሕይወትህ ስኬታማ እንድትሆን ይረዳሃል

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ