የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w25 ሐምሌ ገጽ 32
  • የጥናትህን ውጤት ለሌሎች አካፍል

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የጥናትህን ውጤት ለሌሎች አካፍል
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2025
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • በሥራ ላይ የምታውላቸውን መንፈሳዊ ዕንቁዎች ፈልግ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2024
  • መንፈሳዊ ነገሮች ላይ በማተኮር እረፍት አግኙ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2010
  • ለጥናት የሚረዱ ሐሳቦች
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2023
  • ምሥራቹን ለሌሎች መናገር የምትችለው እንዴት ነው?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2025
w25 ሐምሌ ገጽ 32

ለጥናት የሚረዱ ሐሳቦች

የጥናትህን ውጤት ለሌሎች አካፍል

የጥናት ፕሮግራም መንፈሳችንን ያድስልናል፤ ሆኖም ያገኘናቸውን የሚያበረታቱ መንፈሳዊ ዕንቁዎች ለሌሎች ስናካፍል መንፈሳችን ይበልጥ ይታደሳል። ምሳሌ 11:25 “ሌሎችን [የሚያረካ] እሱ ራሱ ይረካል” ይላል።

ያገኘነውን ትምህርት ለሌሎች ስናካፍል ነጥቦቹን በቀላሉ ማስታወስና ግንዛቤያችንን ማሳደግ እንችላለን። ደግሞም እነዚህ ነጥቦች ሌሎችን ስለሚጠቅሙ እንዲህ ያሉትን ዕንቁዎች ለእነሱ በማካፈላችን እንደሰታለን።—ሥራ 20:35

እስቲ እንዲህ ለማድረግ ሞክር፦ በሚቀጥለው ሳምንት፣ የተማርከውን ነገር ለሌላ ሰው ማካፈል የምትችልበት አጋጣሚ ፈልግ። ለቤተሰብህ አባል፣ በጉባኤህ ውስጥ ላለ ሰው፣ ለሥራ ባልደረባህ፣ አብሮህ ለሚማር ልጅ፣ ለጎረቤትህ ወይም በአገልግሎት ላይ ላገኘኸው ሰው መናገር ትችል ይሆናል። ሐሳቡን ባልተወሳሰበና ግልጽ በሆነ መንገድ በራስህ አባባል ለመግለጽ ጥረት አድርግ።

ይህን አስታውስ፦ የተማርከውን ነገር ለሌሎች የምታካፍለው እነሱን ለማስደመም ሳይሆን ለማበረታታት ሊሆን ይገባል።—1 ቆሮ. 8:1

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ