የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w25 መስከረም ገጽ 32
  • ኢየሱስ “መታዘዝን ተማረ”

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ኢየሱስ “መታዘዝን ተማረ”
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2025
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • “መታዘዝን ተማረ”
    “ተከታዬ ሁን”
  • ተግሣጽን በመቀበል መታዘዝን ተማር
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1992
  • “ታዛዥ ልብ” አለህን?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1998
  • ታዛዥነት—በልጅነት ሊሰጥ የሚገባ አስፈላጊ ትምህርት ነውን?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2001
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2025
w25 መስከረም ገጽ 32

የመጽሐፍ ቅዱስ አገላለጽ

ኢየሱስ “መታዘዝን ተማረ”

ኢየሱስ ቀድሞም ቢሆን ለይሖዋ ታዛዥ ነበር። (ዮሐ. 8:29) ታዲያ መጽሐፍ ቅዱስ “ከደረሰበት መከራ መታዘዝን ተማረ” የሚለው ለምንድን ነው?—ዕብ. 5:8

ኢየሱስ በምድር ላይ ሳለ በሰማይ ላይ አጋጥመውት የማያውቁ ሁኔታዎች አጋጥመውታል። ለምሳሌ ወላጆቹ ለአምላክ ያደሩ ቢሆኑም ፍጹማን አልነበሩም። (ሉቃስ 2:51) ክፉ በሆኑ የሃይማኖት መሪዎችና ፍርደ ገምድል በሆኑ ባለሥልጣናት እጅ ብዙ መከራ ደርሶበታል። (ማቴ. 26:59፤ ማር. 15:15) በተጨማሪም “ራሱን ዝቅ በማድረግ እስከ ሞት ድረስ” ያውም በሚያሠቃይ ሁኔታ እስከመሞት ድረስ “ታዛዥ ሆኗል።”—ፊልጵ. 2:8

ኢየሱስ እነዚህ ነገሮች ስላጋጠሙት በሰማይ ላይ ከነበረው በተለየ ሁኔታ መታዘዝን ተምሯል። በመሆኑም ሊራራልን የሚችል ፍጹም ንጉሥና ሊቀ ካህናት ሊሆን ችሏል። (ዕብ. 4:15፤ 5:9) ኢየሱስ ከደረሰበት መከራ መታዘዝን ከተማረ በኋላ በይሖዋ ዘንድ ይበልጥ ውድ ሆኗል፤ እንዲሁም ይሖዋ በተሻለ መንገድ ሊጠቀምበት ችሏል። እኛም በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ታዛዥ ስንሆን በይሖዋ ዘንድ ይበልጥ ውድ እንሆናለን፤ እንዲሁም እሱ የሚሰጠንን ማንኛውንም ኃላፊነት በተሻለ መንገድ መወጣት እንችላለን።—ያዕ. 1:4

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ