የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ijwex ርዕስ 10
  • ፓስተሩ እሱ መስሏቸው ነበር

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ፓስተሩ እሱ መስሏቸው ነበር
  • የይሖዋ ምሥክሮች ተሞክሮዎች
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ፈጽሞ ባልተጠበቀ ቦታ እውነትን ማግኘት
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2002
  • በጋሪ የሚሰጥ ምሥክርነት በዓለም ዙሪያ ያስገኘው ውጤት
    ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ—2018
  • የዜናው ትኩረት—መካከለኛው ምሥራቅ
    ንቁ!—2015
  • የማረካቸው ፈገግታ ነው!
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2021
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋ ምሥክሮች ተሞክሮዎች
ijwex ርዕስ 10
ሁለት ሰዎች በመቃብር ቦታ ከአንድ የይሖዋ ምሥክር ጋር ሲነጋገሩ። አንደኛው ሰው ከበስተ ጀርባ ወደሚካሄደው የቀብር ሥርዓት እየጠቆመ።

ፓስተሩ እሱ መስሏቸው ነበር

ኦስማን ከባለቤቱና ከሴት ልጁ ጋር ሆኖ ቺሊ ውስጥ በሚገኝ አንድ የመቃብር ስፍራ አካባቢ የጽሑፍ ጋሪ ተጠቅሞ እየሰበከ ነበር። በድንገት፣ ለቀብር የመጡ ብዙ ሰዎች ሙዚቃ እያሰሙ ቦታው ደረሱ። ከሰዎቹ መካከል አንዳንዶቹ ኦስማን ፓስተር ስለመሰላቸው ወደ እሱ መጥተው አቀፉትና “ፓስተር፣ በጊዜ ስለመጣህ እናመሰግናለን፤ እየጠበቅንህ ነበር” አሉት።

ኦስማን እንደተሳሳቱ ሊነግራቸው ቢሞክርም ጫጫታ ስለነበር ሰዎቹ ሊሰሙት አልቻሉም። ለቀስተኞቹ ወደ መቃብሩ ከሄዱ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ የተወሰኑ ሰዎች ተመልሰው በመምጣት “ፓስተር፣ መቃብሩ ጋር ሆነን እየጠበቅንህ ነው” አሉት።

በቦታው የነበረው ጫጫታ ሲቆም፣ ኦስማን ራሱን አስተዋወቃቸውና እዚያ ቦታ የተገኘው ለምን እንደሆነ ነገራቸው። ሰዎቹም ፓስተራቸው ባለመምጣቱ ብስጭታቸውን ከገለጹ በኋላ “ወደ መቃብሩ መጥተህ ከመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የሚያጽናና ሐሳብ ልታካፍለን ትችላለህ?” ብለው ጠየቁት። ኦስማንም በሐሳባቸው ተስማማ።

ወደ መቃብሩ እየሄዱ ሳሉ ኦስማን ስለ ሟቿ አንዳንድ ጥያቄዎችን ከጠየቃቸው በኋላ የትኞቹን ጥቅሶች ሊያነብላቸው እንደሚችል አሰበ። መቃብር ቦታው ጋ ሲደርስ ለሕዝቡ ራሱን አስተዋወቀ፤ እንዲሁም የይሖዋ ምሥክር እንደሆነና ለሰዎች ወንጌልን እንደሚሰብክ ነገራቸው።

ከዚያም ራእይ 21:3, 4ን እና ዮሐንስ 5:28, 29ን በመጥቀስ አምላክ ሰዎች እንዲሞቱ ዓላማው እንዳልነበር አብራራላቸው። እንዲሁም አምላክ በቅርቡ ሙታንን እንደሚያስነሳና በምድር ላይ ለዘላለም የመኖር ተስፋ እንደሚሰጣቸው ነገራቸው። ኦስማን ንግግሩን ከጨረሰ በኋላ ብዙዎቹ ወደ እሱ መጥተው አቀፉትና “የይሖዋን ወንጌል” ስለነገራቸው አመሰገኑት። ከዚያም ኦስማን ወደ ጽሑፍ ጋሪው ተመለሰ።

ከቀብር ሥርዓቱ በኋላ ከለቀስተኞቹ መካከል አንዳንዶቹ ወደ ጽሑፍ ጋሪው መጥተው ኦስማንን እና ቤተሰቡን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጥያቄዎችን ጠየቋቸው። ረጅም ውይይት ካደረጉ በኋላ በጋሪው ላይ የነበሩትን አብዛኞቹን ጽሑፎች ወሰዱ።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ