መዝሙር 50
ራሴን ለአምላክ ለመወሰን ያቀረብኩት ጸሎት
በወረቀት የሚታተመው
1. ጥበብን ይውደድ ልቤ፤
ያስደስትህ ሐሳቤ።
ላንተ ክብር፣ ውዳሴ
ልዘምር ባንደበቴ።
2. ከት’ዛዝህ አልወጣም፤
ሕጎችህን አልረሳም።
አልሳሳም ለንብረቴ፤
ያንተ ነው ውድ አባቴ።
3. ሕይወቴም የአንተው ነው፤
ፈቃድህን እሻለሁ።
ምንም ሳልቆጥብ ራሴን፣
እሰጥሃለሁ ነፍሴን።
(በተጨማሪም መዝ. 40:8ን፣ ዮሐ. 8:29ን እና 2 ቆሮ. 10:5ን ተመልከት።)