መዝሙር 45
ወደፊት ግፋ!
በወረቀት የሚታተመው
1. ወደፊት ግፋ፣ ወደ ጉልምስና!
ችሎታን ማዳበር ያምላክ ፈቃድ ነውና።
ተጣጣር ባገልግሎት ለመሻሻል፤
አምላክ ይባርክሃል።
ሁላችን እንስበክ በጋራ፤
ኢየሱስ ሠርቷል ይህን ሥራ።
አምላክን ተጠጋ፣ ከ’ውነት እንዳትርቅ፤
ሁሌም ተጋደል ለጽድቅ።
2. ወደፊት ግፋ፣ በድፍረት ተናገር!
የዘላለም ምሥራች ለሰው ሁሉ አብስር።
ከቤት ወደ ቤት አዘውትረህ መሥክር፤
ይሖዋ እንዲከብር።
ክፉ ጠላቶች ቢያስፈራሩም፣
አትፍራ ተናገር ለሁሉም።
መንግሥቱ መቅረቡ የምሥራች ነው፤
አስተምር በየቦታው።
3. ወደፊት ግፋ፣ እርዳ ተመላልሰህ፤
ብዙ ሥራ ስላለ ይሻሻል ችሎታህ።
የአምላክም መንፈስ ሁልጊዜ ይምራህ፤
ደስተኛ ትሆናለህ።
ለሰዎች ፍቅር አሳያቸው፤
በቃሉ ይማረክ ልባቸው።
እርዳቸው ፈጣን እድገት እንዲያደርጉ፤
እውነት ይታይ ድምቀቱ።
(በተጨማሪም ፊልጵ. 1:27፤ 3:16ን እና ዕብ. 10:39ን ተመልከት።)