የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • jy ምዕ. 90 ገጽ 212-ገጽ 213 አን. 7
  • “ትንሣኤና ሕይወት”

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • “ትንሣኤና ሕይወት”
  • ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የትንሣኤ ተስፋ
    እስከ ዛሬ ከኖሩት ሁሉ የሚበልጠው ታላቅ ሰው
  • “አምናለሁ”
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2011
  • “አምናለሁ”
    በእምነታቸው ምሰሏቸው
  • ኢየሱስ አልዓዛርን ከሞት አስነሳው
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
ለተጨማሪ መረጃ
ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
jy ምዕ. 90 ገጽ 212-ገጽ 213 አን. 7
ኢየሱስና ማርያም ሌሎች እያዩአቸው ሲያለቅሱ

ምዕራፍ 90

“ትንሣኤና ሕይወት”

ዮሐንስ 11:17-37

  • ኢየሱስ አልዓዛር ከሞተ በኋላ ደረሰ

  • “ትንሣኤና ሕይወት”

ኢየሱስ ከፔሪያ ተነስቶ ከኢየሩሳሌም በስተ ምሥራቅ ሦስት ኪሎ ሜትር ያህል ርቀት ላይ ወደምትገኘው ቢታንያ የተባለች መንደር እየደረሰ ነው። የአልዓዛር እህቶች የሆኑት ማርያምና ማርታ ወንድማቸው በቅርቡ በመሞቱ ሐዘን ላይ ናቸው። እነሱን ለማጽናናት ብዙ ሰዎች ወደ ቤታቸው መጥተዋል።

ማርታ ኢየሱስን ለማግኘት ስትሮጥ

አንድ ሰው ኢየሱስ እየመጣ መሆኑን ለማርታ ሲነግራት እሱን ለመቀበል በፍጥነት ወጣች። ማርታ “ጌታ ሆይ፣ አንተ እዚህ ብትሆን ኖሮ ወንድሜ ባልሞተ ነበር” በማለት እሷና እህቷ ላለፉት አራት ቀናት ሲያስቡት የቆዩትን ነገር ነገረችው። ማርታ ይህን ያለችው ተስፋ ስለሌላት አይደለም። “አምላክ የጠየቅከውን ነገር ሁሉ እንደሚሰጥህ አምናለሁ” በማለት ቀጥላ ተናገረች። (ዮሐንስ 11:21, 22) ኢየሱስ አሁንም ቢሆን ለወንድሟ አንድ ነገር ሊያደርግለት እንደሚችል ተሰምቷታል።

ኢየሱስም “ወንድምሽ ይነሳል” አላት። ኢየሱስ ይህን ሲል ማርታ ወደፊት ምድር ላይ ስለሚከናወነው ትንሣኤ እየተናገረ መሰላት፤ አብርሃምና ሌሎች የአምላክ አገልጋዮችም እንዲህ ዓይነት ተስፋ ነበራቸው። ማርታ በዚህ ተስፋ ላይ ጠንካራ እምነት እንዳላት ስትገልጽ “በመጨረሻው ቀን በትንሣኤ እንደሚነሳ አውቃለሁ” አለች።—ዮሐንስ 11:23, 24

ይሁን እንጂ ኢየሱስ በዚህ ወቅት ሐዘናቸውን የሚያስወግድላቸው ነገር ሊያደርግ ይችላል? አምላክ በሞት ላይ ሥልጣን እንደሰጠው ሲገልጽ ለማርታ እንዲህ አላት፦ “በእኔ የሚያምን ሁሉ ቢሞት እንኳ እንደገና ሕያው ይሆናል፤ በሕይወት ያለና በእኔ የሚያምን ሁሉ ደግሞ ፈጽሞ አይሞትም።”—ዮሐንስ 11:25, 26

ኢየሱስ እንዲህ ሲል በወቅቱ በሕይወት ያሉት ደቀ መዛሙርቱ ፈጽሞ እንደማይሞቱ መናገሩ አይደለም። ለሐዋርያቱ እንደነገራቸው እሱ ራሱ እንኳ መሞቱ አይቀርም። (ማቴዎስ 16:21፤ 17:22, 23) ኢየሱስ በእሱ ማመን ወደ ዘላለም ሕይወት ሊመራ እንደሚችል ማጉላት ፈልጓል። ብዙዎች እንዲህ ያለውን ሕይወት የሚያገኙት ከሞት ሲነሱ ነው። ሆኖም ይህ ሥርዓት ሲያበቃ በሕይወት የሚኖሩ ሌሎች ታማኝ የአምላክ አገልጋዮች ፈጽሞ ሞትን ላያዩ ይችላሉ። ያም ሆነ ይህ በኢየሱስ የሚያምን ሁሉ፣ ሞቶ እንደማይቀር እርግጠኛ መሆን ይችላል።

ኢየሱስ “ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ” በማለት ተናገረ፤ ታዲያ ከሞተ ቀናት ያለፉትን አልዓዛርን ሊያስነሳው ይችላል? ኢየሱስ “ይህን ታምኛለሽ?” በማለት ማርታን ጠየቃት። እሷም “አዎ፣ ጌታ ሆይ፣ አንተ ወደ ዓለም የሚመጣው የአምላክ ልጅ ክርስቶስ መሆንህን አምናለሁ” አለችው። ኢየሱስ በዚያው ዕለት የሆነ ነገር ሊያደርግ እንደሚችል ስላመነች በፍጥነት ወደ ቤት በመሄድ እህቷን ለብቻዋ ጠርታ “መምህሩ መጥቷል፤ እየጠራሽ ነው” አለቻት። (ዮሐንስ 11:25-28) በዚህ ጊዜ ማርያም ከቤት ወጣች፤ እዚያ ያሉት ሰዎችም ወደ አልዓዛር መቃብር የምትሄድ ስለመሰላቸው ተከተሏት።

ማርያም ግን ወደ ኢየሱስ በመሄድ እግሩ ላይ ወድቃ እያለቀሰች “ጌታ ሆይ፣ አንተ እዚህ ብትሆን ኖሮ ወንድሜ ባልሞተ ነበር” በማለት እህቷ የተናገረችውን ደገመችው። ኢየሱስ ማርያምና አብረዋት የመጡት ሰዎች ሲያለቅሱ ሲያይ እጅግ አዘነ፤ ተረበሸም፤ እንዲያውም እንባውን አፈሰሰ። በቦታው ያሉት ሰዎች ይህን ሲያዩ ተገረሙ። ሆኖም አንዳንዶች ‘ኢየሱስ የዓይነ ስውርን ዓይን ማብራት ከቻለ ይሄኛውንም እንዳይሞት ማድረግ አይችልም ነበር?’ አሉ።—ዮሐንስ 11:32, 37

  • ኢየሱስ ወደ ቢታንያ ሲቃረብ ምን ዓይነት ሁኔታ አጋጠመው?

  • ማርታ በትንሣኤ ለማመን ምን መሠረት አላት?

  • ኢየሱስ ከአልዓዛር ጋር በተያያዘ ሊያደርግ የሚችለው ነገር እንዳለ የጠቆመው እንዴት ነው?

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ