-
ዘዳግም 33:13-17አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
13 ስለ ዮሴፍ እንዲህ አለ፦+
“ይሖዋ ከሰማይ በሚወርዱ ምርጥ ነገሮች፣
በጤዛና ከታች በሚመነጩ ውኃዎች+
ምድሩን ይባርክ፤+
14 እንዲሁም ፀሐይ በምታስገኛቸው ምርጥ ነገሮች፣
በየወሩ በሚገኝ ምርጥ ፍሬ፣+
15 ጥንታዊ ከሆኑ ተራሮች* በሚገኙ ምርጥ ነገሮች፣+
ጸንተው ከሚኖሩት ኮረብቶች በሚገኙ ምርጥ ነገሮች፣
16 ከምድር በሚገኙ ምርጥ ነገሮችና ምድርን በሞሉ ምርጥ ነገሮች፣+
በቁጥቋጦው ውስጥ በተገለጠው በእሱ ሞገስ ይባርክ።+
እነዚህ ሁሉ በዮሴፍ ራስ ላይ፣
ከወንድሞቹ መካከል ተነጥሎ በወጣው አናት ላይ ይውረዱ።+
17 ግርማው እንደ በኩር በሬ ነው፤
ቀንዶቹም የዱር በሬ ቀንድ ናቸው።
በእነሱም ሰዎችን፣
ሕዝቦችን ሁሉ እስከ ምድር ዳርቻ ይገፋል።*
እነሱ የኤፍሬም አሥር ሺዎች ናቸው፤+
የምናሴም ሺዎች ናቸው።”
-