-
ዘዳግም 19:14አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
14 “አምላክህ ይሖዋ እንድትወርሳት በሚሰጥህ ምድር ውስጥ ርስትህን በምትቀበልበት ጊዜ የቀድሞ አባቶችህ የከለሉትን ወሰን በማለፍ የባልንጀራህን የድንበር ምልክት አትንካ።+
-
-
ዘዳግም 27:17አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
17 “‘የጎረቤቱን የወሰን ምልክት የሚገፋ የተረገመ ይሁን።’+ (ሕዝቡም ሁሉ ‘አሜን!’ ይላል።)
-
-
ምሳሌ 23:10አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
10 የጥንቱን የወሰን ምልክት ከቦታው አታንቀሳቅስ፤+
ደግሞም አባት የሌላቸውን ልጆች መሬት አትያዝ።
-
-
ሆሴዕ 5:10አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
10 የይሁዳ መኳንንት ወሰን እንደሚገፉ ሰዎች ናቸው።+
በእነሱ ላይ ቁጣዬን እንደ ውኃ አፈሳለሁ።
-