ዘዳግም 33:29 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 29 እስራኤል ሆይ፣ ደስተኛ ነህ!+ የይሖዋን ማዳን ያየ፣+እንደ አንተ ያለ ሕዝብ ማን አለ?+እሱ የሚከልል ጋሻህና+ታላቅ ሰይፍህ ነው፤ ጠላቶችህ በፊትህ ይንቀጠቀጣሉ፤+አንተም በጀርባቸው* ላይ ትራመዳለህ።” 2 ሳሙኤል 22:3 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 3 አምላኬ የምሸሸግበት ዓለቴ ነው፤+ጋሻዬ፣+ የመዳኔ ቀንድና* አስተማማኝ መጠጊያዬ ነው፤+መሸሻዬና+ አዳኜ ነው፤+ አንተ ከዓመፅ ታድነኛለህ። መዝሙር 144:2 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 2 እሱ ታማኝ ፍቅር የሚያሳየኝ አምላኬና ምሽጌ፣አስተማማኝ መጠጊያዬና ታዳጊዬ፣ጋሻዬና መጠለያዬ፣+ሕዝቦችን ከበታቼ የሚያስገዛልኝ አምላኬ ነው።+
29 እስራኤል ሆይ፣ ደስተኛ ነህ!+ የይሖዋን ማዳን ያየ፣+እንደ አንተ ያለ ሕዝብ ማን አለ?+እሱ የሚከልል ጋሻህና+ታላቅ ሰይፍህ ነው፤ ጠላቶችህ በፊትህ ይንቀጠቀጣሉ፤+አንተም በጀርባቸው* ላይ ትራመዳለህ።”