-
ኢዮብ 38:8-10አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
8 ባሕሩ ከማህፀን አፈትልኮ በወጣ ጊዜ፣
በር የዘጋበት ማን ነው?+
9 ደመና ባለበስኩት ጊዜ፣
በድቅድቅ ጨለማም በጠቀለልኩት ጊዜ፣
10 በላዩም ድንበሬን በወሰንኩ ጊዜ፣
መቀርቀሪያዎችና በሮች ባደረግኩለት ጊዜ፣+
-
መዝሙር 33:7አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
7 የባሕርን ውኃዎች እንደ ግድብ ያከማቻል፤+
የሚናወጠውንም ውኃ በማከማቻ ቦታ ይሰበስባል።
-
-
ምሳሌ 8:29አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
29 የባሕሩ ውኃ
ከትእዛዙ አልፎ እንዳይሄድ በደነገገ ጊዜ፣+
የምድርን መሠረቶች ባቆመ* ጊዜ፣
-
ኤርምያስ 5:22አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
22 ‘እኔን አትፈሩም?’ ይላል ይሖዋ፤
‘በፊቴስ ልትሸበሩ አይገባም?
ውኃው አልፎ እንዳይሄድ፣ በማይሻር ድንጋጌ
አሸዋውን የባሕሩ ወሰን አድርጌ የሠራሁት እኔ ነኝ።
ሞገዶቹ ቢናወጡም ጥሰው መሄድ አይችሉም፤
ቢያስገመግሙም ከዚያ አልፈው መሄድ አይችሉም።+
-
-
-
-
-