የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • 2 ሳሙኤል 22:8-16
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    •  8 ምድርም ወዲያና ወዲህ ትናወጥና ትንቀጠቀጥ ጀመር፤+

      የሰማያት መሠረቶች ተንቀጠቀጡ፤+

      እሱ ስለተቆጣም ራዱ።+

       9 ከአፍንጫው ጭስ ወጣ፤

      የሚባላም እሳት ከአፉ ወጣ፤+

      ፍምም ከእሱ ፈለቀ።

      10 ወደ ታች ሲወርድ ሰማያት እንዲያጎነብሱ አደረገ፤+

      ከእግሮቹም በታች ጥቅጥቅ ያለ ደመና ነበር።+

      11 በኪሩብ ላይ ተቀምጦ+ እየበረረ መጣ።

      በመንፈስ ክንፎችም* ላይ ሆኖ ይታይ ነበር።+

      12 ከዚያም ጨለማን በዙሪያው እንደ መጠለያ አደረገ፣+

      ጨለማውም ጥቁር ውኃና ጥቅጥቅ ያለ ደመና ነበረው።

      13 በፊቱ ካለው ብርሃን ፍም ፈለቀ።

      14 ከዚያም ይሖዋ ከሰማይ ያንጎደጉድ ጀመር፤+

      ልዑሉ አምላክ ድምፁን አሰማ።+

      15 ፍላጻዎቹን+ አስፈንጥሮ በታተናቸው፤

      መብረቁን አብርቆ ግራ አጋባቸው።+

      16 በይሖዋ ተግሣጽ፣ ከአፍንጫውም በሚወጣው ኃይለኛ እስትንፋስ+

      የባሕር ወለሎች ታዩ፤+

      የምድር መሠረቶችም ተገለጡ።

  • መዝሙር 77:18
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 18 የነጎድጓድህ ድምፅ+ እንደ ሠረገላ ድምፅ ነበር፤

      የመብረቅ ብልጭታዎች በዓለም* ላይ አበሩ፤+

      ምድር ተናወጠች፤ ደግሞም ተንቀጠቀጠች።+

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ