-
ዘሌዋውያን 26:29አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
29 በመሆኑም የወንድ ልጆቻችሁን ሥጋ ትበላላችሁ፤ የሴት ልጆቻችሁንም ሥጋ ትበላላችሁ።+
-
-
ዘዳግም 28:53-57አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
53 ከሚያስጨንቀው ከበባና ጠላትህ በአንተ ላይ ከሚያደርሰው ሥቃይ የተነሳ አምላክህ ይሖዋ የሰጠህን የሆድህን ፍሬ ይኸውም የወንዶችና የሴቶች ልጆችህን ሥጋ ትበላለህ።+
54 “ሌላው ቀርቶ በመካከልህ ያለ በምቾትና በቅምጥልነት ይኖር የነበረ ሰው እንኳ በወንድሙ፣ በሚወዳት ሚስቱ ወይም በተረፉት ልጆቹ ላይ ይጨክናል፤ 55 ከሚበላው የልጆቹ ሥጋ ላይ ምንም ነገር አያካፍላቸውም፤ ምክንያቱም ከሚያስጨንቀው ከበባና ጠላትህ በከተሞችህ ላይ ከሚያመጣው ሥቃይ የተነሳ የሚተርፈው ምንም ነገር አይኖረውም።+ 56 ከቅምጥልነቷ የተነሳ መሬት ለመርገጥ እንኳ ትጸየፍ የነበረች+ በመካከልህ ያለች ቅምጥልና በምቾት የምትኖር ሴትም በምትወደው ባሏ፣ በወንድ ልጇ ወይም በሴት ልጇ ላይ ትጨክናለች፤ 57 ሌላው ቀርቶ ከወሊድ በኋላ ከእግሮቿ መካከል በሚወጣው ነገር ሁሉና በምትወልዳቸው ልጆች ላይ ትጨክናለች፤ ምክንያቱም ከሚያስጨንቀው ከበባና ጠላትህ በከተሞችህ ላይ ከሚያመጣው ሥቃይ የተነሳ በድብቅ ትበላቸዋለች።
-
-
ኢዮብ 39:14-16አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
14 እንቁላሎቿን መሬት ላይ ትጥላለች፤
በአፈርም ውስጥ ታሞቃቸዋለች።
15 እግር ሊሰብራቸው፣
የዱር አውሬም ሊረግጣቸው እንደሚችል አታስብም።
16 ልጆቿ የራሷ ያልሆኑ ይመስል ትጨክንባቸዋለች፤+
ድካሜ ሁሉ ከንቱ ይሆናል የሚል ስጋት አያድርባትም።
-