መዝሙር 80:14-16 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 14 የሠራዊት አምላክ ሆይ፣ እባክህ ተመለስ። ከሰማይ ወደ ታች እይ፤ ተመልከትም! ይህችን የወይን ተክል ተንከባከባት፤+15 ቀኝ እጅህ የተከላትን ግንድ*+ በእንክብካቤ ያዛት፤ለራስህ ስትል ያጠነከርከውንም ልጅ* ተመልከት።+ 16 እሷ ተቆርጣ በእሳት ተቃጥላለች።+ ሕዝቡ ከተግሣጽህ* የተነሳ ይጠፋል። ኢሳይያስ 5:24 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 24 የእሳት ነበልባል ገለባን እንደሚበላ፣የደረቀም ሣር በነበልባል በንኖ እንደሚጠፋየእነሱም ሥር ይበሰብሳል፤አበባቸውም ልክ እንደ ዱቄት በየቦታው ይበናል፤ምክንያቱም እነሱ የሠራዊት ጌታ የሆነውን የይሖዋን ሕግ* ለመቀበል አሻፈረን ብለዋል፣የእስራኤል ቅዱስ የተናገረውንም ቃል ንቀዋል።+ ኤርምያስ 7:20 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 20 ስለዚህ ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ ‘እነሆ፣ ንዴቴና ቁጣዬ በዚህ ቦታ፣ በሰውና በእንስሳ፣ በዱር ዛፎችና በምድሪቱ ፍሬ ላይ ይፈስሳል፤+ ቁጣዬ ይነድዳል፤ ፈጽሞም አይጠፋም።’+ ሕዝቅኤል 20:47 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 47 በደቡብ ለሚገኘው ደን እንዲህ በል፦ ‘የይሖዋን ቃል ስማ። ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ “እነሆ፣ በአንተ ላይ እሳት አነዳለሁ፤+ እሳቱም በአንተ ውስጥ ያለውን የለመለመውንና ደረቁን ዛፍ ሁሉ ይበላል። የሚንቦገቦገው ነበልባል አይጠፋም፤+ እሱም ከደቡብ እስከ ሰሜን ያለውን ፊት* ሁሉ ይለበልባል።
14 የሠራዊት አምላክ ሆይ፣ እባክህ ተመለስ። ከሰማይ ወደ ታች እይ፤ ተመልከትም! ይህችን የወይን ተክል ተንከባከባት፤+15 ቀኝ እጅህ የተከላትን ግንድ*+ በእንክብካቤ ያዛት፤ለራስህ ስትል ያጠነከርከውንም ልጅ* ተመልከት።+ 16 እሷ ተቆርጣ በእሳት ተቃጥላለች።+ ሕዝቡ ከተግሣጽህ* የተነሳ ይጠፋል።
24 የእሳት ነበልባል ገለባን እንደሚበላ፣የደረቀም ሣር በነበልባል በንኖ እንደሚጠፋየእነሱም ሥር ይበሰብሳል፤አበባቸውም ልክ እንደ ዱቄት በየቦታው ይበናል፤ምክንያቱም እነሱ የሠራዊት ጌታ የሆነውን የይሖዋን ሕግ* ለመቀበል አሻፈረን ብለዋል፣የእስራኤል ቅዱስ የተናገረውንም ቃል ንቀዋል።+
20 ስለዚህ ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ ‘እነሆ፣ ንዴቴና ቁጣዬ በዚህ ቦታ፣ በሰውና በእንስሳ፣ በዱር ዛፎችና በምድሪቱ ፍሬ ላይ ይፈስሳል፤+ ቁጣዬ ይነድዳል፤ ፈጽሞም አይጠፋም።’+
47 በደቡብ ለሚገኘው ደን እንዲህ በል፦ ‘የይሖዋን ቃል ስማ። ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ “እነሆ፣ በአንተ ላይ እሳት አነዳለሁ፤+ እሳቱም በአንተ ውስጥ ያለውን የለመለመውንና ደረቁን ዛፍ ሁሉ ይበላል። የሚንቦገቦገው ነበልባል አይጠፋም፤+ እሱም ከደቡብ እስከ ሰሜን ያለውን ፊት* ሁሉ ይለበልባል።