-
ማቴዎስ 22:23-28አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
23 በዚያኑ ዕለት፣ በትንሣኤ የማያምኑት+ ሰዱቃውያን መጥተው እንዲህ ሲሉ ጠየቁት፦+ 24 “መምህር፣ ሙሴ ‘አንድ ሰው ልጅ ሳይወልድ ቢሞት ወንድሙ የሟቹን ሚስት ማግባትና ለወንድሙ ዘር መተካት አለበት’ ብሏል።+ 25 በእኛ ዘንድ ሰባት ወንድማማቾች ነበሩ። የመጀመሪያው ሚስት አግብቶ ልጅ ሳይወልድ በመሞቱ ወንድሙ የሟቹን ሚስት አገባ። 26 ሁለተኛውም ሆነ ሦስተኛው እስከ ሰባተኛው ድረስ ልጅ ሳይወልዱ ሞቱ። 27 በመጨረሻም ሴትየዋ ሞተች። 28 እንግዲህ ሁሉም ስላገቧት በትንሣኤ ከሰባቱ ለየትኛው ሚስት ትሆናለች?”
-
-
ሉቃስ 20:27-33አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
27 ሆኖም በትንሣኤ ከማያምኑት+ ሰዱቃውያን መካከል አንዳንዶቹ መጥተው ጥያቄ አቀረቡለት፦+ 28 “መምህር፣ ሙሴ ‘አንድ ሰው ሚስት አግብቶ ልጅ ሳይወልድ ቢሞት ወንድሙ ሚስትየዋን አግብቶ ለወንድሙ ዘር መተካት አለበት’ ብሎ ጽፎልናል።+ 29 እንግዲህ ሰባት ወንድማማቾች ነበሩ። የመጀመሪያው ሚስት አገባ፤ ሆኖም ልጅ ሳይወልድ ሞተ። 30 ሁለተኛውም እንደዚሁ፤ 31 ሦስተኛውም አገባት። በዚሁ አኳኋን ሰባቱም አግብተዋት ልጆች ሳይወልዱ ሞቱ። 32 በመጨረሻም ሴትየዋ ሞተች። 33 እንግዲህ ሰባቱም ስላገቧት በትንሣኤ ለየትኛው ሚስት ትሆናለች?”
-