የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • ዛሬ

ሐሙስ፣ ሐምሌ 24

ይሖዋ እረኛዬ ነው። የሚጎድልብኝ ነገር የለም።—መዝ. 23:1

በመዝሙር 23 ላይ ዳዊት በይሖዋ ፍቅርና እንክብካቤ ላይ ያለውን የመተማመን ስሜት ገልጿል። ዳዊት በእሱና በእረኛው በይሖዋ መካከል ስላለው የጠበቀ ዝምድና ተናግሯል። ዳዊት የይሖዋን አመራር በመከተሉ የደህንነት ስሜት ተሰምቶታል፤ እንዲሁም በእሱ ሙሉ በሙሉ ይተማመን ነበር። ዳዊት የይሖዋ ፍቅር በሕይወት ዘመኑ ሁሉ እንደሚከተለው ያውቅ ነበር። ይህን ያህል እንዲተማመን ያደረገው ምንድን ነው? ዳዊት የሚያስፈልገውን ነገር በሙሉ ይሖዋ ስላሟላለት በደንብ እንደተንከባከበው ተሰምቶታል። ዳዊት የይሖዋን ወዳጅነትና ሞገስ አግኝቷል። በመሆኑም ወደፊት ምንም ቢመጣ የይሖዋ እንክብካቤ እንደማይቋረጥበት እርግጠኛ ነበር። ዳዊት በይሖዋ ፍቅርና እንክብካቤ ላይ ጠንካራ እምነት ስለነበረው ማንኛውንም ጭንቀት አሸንፎ ጥልቅ ደስታና እርካታ ማግኘት ችሏል።—መዝ. 16:11፤ w24.01 28-29 አን. 12-13

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ዓርብ፣ ሐምሌ 25

እኔ እስከ ሥርዓቱ መደምደሚያ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።—ማቴ. 28:20

ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ በበርካታ አገሮች ያሉ የይሖዋ ሕዝቦች የስብከቱን ሥራ ለማከናወን የሚያስችል መጠነኛ ሰላምና ነፃነት አግኝተዋል። እንዲያውም ሥራው በእጅጉ ተስፋፍቷል። በዛሬው ጊዜ የበላይ አካል አባላት የክርስቶስን አመራር ለማግኘት ጥረት ማድረጋቸውን ቀጥለዋል። ለወንድሞች የሚሰጡት መመሪያ የይሖዋንና የኢየሱስን አመለካከት የሚያንጸባርቅ እንዲሆን ይፈልጋሉ። የወረዳ የበላይ ተመልካቾችና ሽማግሌዎች ደግሞ ለጉባኤዎች መመሪያ ይሰጣሉ። ቅቡዓን ሽማግሌዎች በክርስቶስ ‘ቀኝ እጅ’ ውስጥ ናቸው። (ራእይ 2:1) እርግጥ ነው፣ እነዚህ ሽማግሌዎች ፍጹማን ስላልሆኑ ስህተት መሥራታቸው አይቀርም። ሙሴና ኢያሱ ስህተት የሠሩባቸው ጊዜያት ነበሩ፤ ሐዋርያትም እንደዚያው። (ዘኁ. 20:12፤ ኢያሱ 9:14, 15፤ ሮም 3:23) ያም ቢሆን፣ ክርስቶስ ታማኙን ባሪያና የተሾሙ ሽማግሌዎችን በጥንቃቄ እየመራቸው ነው። ደግሞም እንዲህ ማድረጉን ይቀጥላል። በመሆኑም ኃላፊነት ባላቸው ወንድሞች አማካኝነት በሚሰጠን አመራር ላይ ለመተማመን የሚያበቃ አጥጋቢ ምክንያት አለን። w24.02 23 አን. 13-14

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ቅዳሜ፣ ሐምሌ 26

የተወደዳችሁ ልጆቹ በመሆን አምላክን የምትመስሉ ሁኑ።—ኤፌ. 5:1

በዛሬው ጊዜ ቅንዓት፣ አመስጋኝነትና ፍቅር በሚንጸባረቅበት መንገድ ስለ ይሖዋ በመናገር እሱን ማስደሰት እንችላለን። አገልግሎት ስንወጣ ዋነኛው ዓላማችን ሰዎች ወደ ይሖዋ እንዲቀርቡ እንዲሁም ለሰማዩ አባታችን የእኛ ዓይነት አመለካከት እንዲያዳብሩ መርዳት እንደሆነ አንዘነጋም። (ያዕ. 4:8) ለሰዎች መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ይሖዋ ምን እንደሚል ማለትም እንደ ፍቅር፣ ፍትሕ፣ ጥበብና ኃይል ያሉትን ባሕርያቱን እንዴት አድርጎ እንደሚገልጽ ስናሳያቸው ደስ ይለናል። በተጨማሪም ይሖዋን ለመምሰል የቻልነውን ሁሉ በማድረግ እሱን ማወደስና ማስደሰት እንችላለን። እንዲህ ስናደርግ በዚህ ክፉ ዓለም ውስጥ ካሉት ሰዎች የተለየን እንደሆንን ይታያል። (ማቴ. 5:14-16) ሰዎች የተለየን መሆናችንን ሲያስተውሉ ምክንያቱን ማወቅ ይፈልጉ ይሆናል። በዕለት ተዕለት ሕይወታችን ከሰዎች ጋር ስንገናኝ የተለየን የሆንበትን ምክንያት ልናብራራላቸው እንችላለን። በዚህም የተነሳ ቅን ልብ ያላቸው ሰዎች ወደ አምላካችን ለመቅረብ ይነሳሳሉ። በእነዚህ መንገዶች ይሖዋን ስናወድስ ልቡን እናስደስታለን።—1 ጢሞ. 2:3, 4፤ w24.02 10 አን. 7

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ