የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • ዛሬ

ረቡዕ፣ ሐምሌ 23

ከፍተኛ ችግር ውስጥ ከተታችሁኝ።—ዘፍ. 34:30

ያዕቆብ ብዙ መከራዎች አጋጥመውታል። ሁለቱ የያዕቆብ ልጆች ስምዖንና ሌዊ ቤተሰባቸውን ያሳፈሩ ከመሆኑም ሌላ በይሖዋ ስም ላይ ነቀፋ አምጥተዋል። በተጨማሪም ያዕቆብ የሚወዳት ሚስቱ ራሔል ሁለተኛ ልጇን ስትወልድ ሞተችበት። በኋላም ከባድ ረሃብ በመከሰቱ ያዕቆብ በስተ እርጅናው ወደ ግብፅ ለመሰደድ ተገደደ። (ዘፍ. 35:16-19፤ 37:28፤ 45:9-11, 28) ያዕቆብ ይህ ሁሉ መከራ ቢደርስበትም በይሖዋና እሱ በገባው ቃል ላይ ያለውን እምነት አላጣም። ይሖዋም የእሱ ሞገስ እንዳልተለየው ለያዕቆብ አረጋግጦለታል። ለምሳሌ ይሖዋ ያዕቆብን በቁሳዊ አበልጽጎታል። በተጨማሪም ያዕቆብ፣ ‘ሞቷል’ ብሎ ከሚያስበው ልጁ ጋር ከረጅም ጊዜ በኋላ ሲገናኝ ይሖዋን ምን ያህል አመስግኖት ሊሆን እንደሚችል እስቲ አስበው! ያዕቆብ ከይሖዋ ጋር የጠበቀ ወዳጅነት ስለነበረው ያጋጠመውን መከራ በጽናት መወጣት ችሏል። (ዘፍ. 30:43፤ 32:9, 10፤ 46:28-30) እኛም ከይሖዋ ጋር የጠበቀ ወዳጅነት ካለን ያልተጠበቁ ፈተናዎችን በጽናት መወጣት እንችላለን። w23.04 15 አን. 6-7

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ሐሙስ፣ ሐምሌ 24

ይሖዋ እረኛዬ ነው። የሚጎድልብኝ ነገር የለም።—መዝ. 23:1

በመዝሙር 23 ላይ ዳዊት በይሖዋ ፍቅርና እንክብካቤ ላይ ያለውን የመተማመን ስሜት ገልጿል። ዳዊት በእሱና በእረኛው በይሖዋ መካከል ስላለው የጠበቀ ዝምድና ተናግሯል። ዳዊት የይሖዋን አመራር በመከተሉ የደህንነት ስሜት ተሰምቶታል፤ እንዲሁም በእሱ ሙሉ በሙሉ ይተማመን ነበር። ዳዊት የይሖዋ ፍቅር በሕይወት ዘመኑ ሁሉ እንደሚከተለው ያውቅ ነበር። ይህን ያህል እንዲተማመን ያደረገው ምንድን ነው? ዳዊት የሚያስፈልገውን ነገር በሙሉ ይሖዋ ስላሟላለት በደንብ እንደተንከባከበው ተሰምቶታል። ዳዊት የይሖዋን ወዳጅነትና ሞገስ አግኝቷል። በመሆኑም ወደፊት ምንም ቢመጣ የይሖዋ እንክብካቤ እንደማይቋረጥበት እርግጠኛ ነበር። ዳዊት በይሖዋ ፍቅርና እንክብካቤ ላይ ጠንካራ እምነት ስለነበረው ማንኛውንም ጭንቀት አሸንፎ ጥልቅ ደስታና እርካታ ማግኘት ችሏል።—መዝ. 16:11፤ w24.01 28-29 አን. 12-13

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ዓርብ፣ ሐምሌ 25

እኔ እስከ ሥርዓቱ መደምደሚያ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።—ማቴ. 28:20

ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ በበርካታ አገሮች ያሉ የይሖዋ ሕዝቦች የስብከቱን ሥራ ለማከናወን የሚያስችል መጠነኛ ሰላምና ነፃነት አግኝተዋል። እንዲያውም ሥራው በእጅጉ ተስፋፍቷል። በዛሬው ጊዜ የበላይ አካል አባላት የክርስቶስን አመራር ለማግኘት ጥረት ማድረጋቸውን ቀጥለዋል። ለወንድሞች የሚሰጡት መመሪያ የይሖዋንና የኢየሱስን አመለካከት የሚያንጸባርቅ እንዲሆን ይፈልጋሉ። የወረዳ የበላይ ተመልካቾችና ሽማግሌዎች ደግሞ ለጉባኤዎች መመሪያ ይሰጣሉ። ቅቡዓን ሽማግሌዎች በክርስቶስ ‘ቀኝ እጅ’ ውስጥ ናቸው። (ራእይ 2:1) እርግጥ ነው፣ እነዚህ ሽማግሌዎች ፍጹማን ስላልሆኑ ስህተት መሥራታቸው አይቀርም። ሙሴና ኢያሱ ስህተት የሠሩባቸው ጊዜያት ነበሩ፤ ሐዋርያትም እንደዚያው። (ዘኁ. 20:12፤ ኢያሱ 9:14, 15፤ ሮም 3:23) ያም ቢሆን፣ ክርስቶስ ታማኙን ባሪያና የተሾሙ ሽማግሌዎችን በጥንቃቄ እየመራቸው ነው። ደግሞም እንዲህ ማድረጉን ይቀጥላል። በመሆኑም ኃላፊነት ባላቸው ወንድሞች አማካኝነት በሚሰጠን አመራር ላይ ለመተማመን የሚያበቃ አጥጋቢ ምክንያት አለን። w24.02 23 አን. 13-14

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ