የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • ዛሬ

እሁድ፣ ነሐሴ 3

እርስ በርስ እንበረታታ።—ዕብ. 10:25

በስብሰባ ላይ ሐሳብ ስለመስጠት ስታስቡ እንኳ በጣም የሚያስፈራችሁ ከሆነስ? በደንብ መዘጋጀታችሁ ሊረዳችሁ ይችላል። (ምሳሌ 21:5) ትምህርቱን ከራሳችሁ ጋር ይበልጥ ባዋሃዳችሁት መጠን ሐሳብ መስጠት ይበልጥ ይቀላችኋል። በተጨማሪም አጭር መልስ ለመመለስ ሞክሩ። (ምሳሌ 15:23፤ 17:27) መልሳችሁ አጭር ከሆነ ያን ያህል አያስፈራችሁም። በራሳችሁ አባባል አጭር መልስ መመለሳችሁ በደንብ እንደተዘጋጃችሁና ትምህርቱን በሚገባ እንደተረዳችሁት ያሳያል። እነዚህን ምክሮች ተግባራዊ ለማድረግ ጥረት ብታደርጉም ከአንዴ ወይም ከሁለቴ በላይ ሐሳብ መስጠት የሚያስፈራችሁ ቢሆንስ? አቅማችሁ የፈቀደውን ነገር ለማድረግ የምታደርጉትን ጥረት ይሖዋ ከፍ አድርጎ እንደሚመለከተው እርግጠኛ ሁኑ። (ሉቃስ 21:1-4) ምርጣችንን መስጠት ማለት ከአቅማችን በላይ መጣጣር ማለት አይደለም። (ፊልጵ. 4:5) ምን ማድረግ እንደምትችሉ አስቡ፤ ግብ አውጡ፤ እንዲሁም መረጋጋት እንድትችሉ ጸልዩ። መጀመሪያ ላይ፣ አንድ አጭር መልስ ብቻ ለመመለስ ግብ ማውጣታችሁ በቂ ሊሆን ይችላል። w23.04 21 አን. 6-8

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ሰኞ፣ ነሐሴ 4

ጥሩር እንልበስ፤ . . . ራስ ቁር እንድፋ።—1 ተሰ. 5:8

ሐዋርያው ጳውሎስ ዝግጁ ከሆኑና የጦር ትጥቅ ከለበሱ ወታደሮች ጋር አመሳስሎናል። አንድ ወታደር በማንኛውም ጊዜ ለጦርነት ዝግጁ እንዲሆን ይጠበቅበታል። የእኛም ሁኔታ ተመሳሳይ ነው። የእምነትንና የፍቅርን ጥሩር በመልበስ እንዲሁም ተስፋን እንደ ራስ ቁር በመድፋት የይሖዋን ቀን ዝግጁ ሆነን መጠበቅ እንችላለን። ጥሩር የአንድን ወታደር ልብ ከጉዳት ይጠብቅለታል። እምነትና ፍቅርም ምሳሌያዊ ልባችንን ይጠብቁልናል። አምላክን ማገልገላችንንና ኢየሱስን መከተላችንን እንድንቀጥል ይረዱናል። እምነት ካለን ይሖዋ እሱን በሙሉ ልባችን በመፈለጋችን ወሮታ እንደሚከፍለን እርግጠኞች እንሆናለን። (ዕብ. 11:6) እምነት፣ መከራ ቢደርስብንም እንኳ ለመሪያችን ለኢየሱስ ምንጊዜም ታማኝ እንድንሆን ያነሳሳናል። ስደት ወይም የኢኮኖሚ ችግር ቢያጋጥማቸውም ንጹሕ አቋማቸውን ከጠበቁ በዘመናችን ያሉ ታማኝ የአምላክ አገልጋዮች በመማር የሚያጋጥሙንን ተፈታታኝ ሁኔታዎች ለመቋቋም የሚያስችል እምነት መገንባት እንችላለን። በተጨማሪም መንግሥቱን ለማስቀደም ሲሉ አኗኗራቸውን ቀላል ያደረጉ ክርስቲያኖችን ምሳሌ በመከተል ከፍቅረ ነዋይ ወጥመድ መራቅ እንችላለን። w23.06 10 አን. 8-9

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ማክሰኞ፣ ነሐሴ 5

ነፋስን የሚጠባበቅ አይዘራም።—መክ. 11:4

ራስን መግዛት፣ ስሜትንና ድርጊትን የመቆጣጠር ችሎታ ነው። ግባችን ላይ ለመድረስ ራስን መግዛት ያስፈልገናል። በተለይ እዚያ ግብ ላይ መድረስ ከባድ ከሆነ ወይም ተነሳሽነት ካጣን ራሳችንን መግዛታችን አስፈላጊ ነው። ራስን መግዛት የአምላክ መንፈስ ፍሬ ገጽታ እንደሆነ አትዘንጋ። በመሆኑም ይህን አስፈላጊ ባሕርይ ማዳበር እንድትችል መንፈስ ቅዱስን እንዲሰጥህ ይሖዋን ጠይቀው። (ሉቃስ 11:13፤ ገላ. 5:22, 23) ሁኔታዎች ሙሉ በሙሉ እስኪስተካከሉ አትጠብቅ። በዚህ ዓለም ውስጥ ሁሉ ነገር ሊስተካከልልን እንደማይችል የታወቀ ነው። ሁሉ ነገር እስኪስተካከል ከጠበቅን ግባችን ላይ ፈጽሞ ላንደርስ እንችላለን። ግባችን ላይ መድረስ በጣም አስቸጋሪ እንደሆነ ከተሰማን ተነሳሽነታችን ሊጠፋ ይችላል። የአንተም ሁኔታ እንደዚያ ከሆነ ግብህን በትንሽ በትንሹ ልትከፋፍለው ትችል ይሆን? ለምሳሌ ግብህ አንድ ክርስቲያናዊ ባሕርይ ማዳበር ከሆነ መጀመሪያ ላይ ይህን ባሕርይ በትናንሽ መንገዶች ለማንጸባረቅ ለምን አትሞክርም? ግብህ መጽሐፍ ቅዱስን አንብቦ መጨረስ ከሆነ ደግሞ ለጥቂት ደቂቃዎች ብቻ በማንበብ ለምን አትጀምርም? w23.05 29 አን. 11-13

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ