የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w14 8/1 ገጽ 5
  • አምላክ ስሜትህን ይረዳልሃል

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • አምላክ ስሜትህን ይረዳልሃል
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2014
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • አ ም ላ ክ በእርግጥ ያውቅሃልን?
    መጠበቂያ ግንብ—1993
  • አምላክ ስሜትህን ይረዳልሃል?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2018
  • ግሩምና ድንቅ ሆነን ተፈጥረናል
    ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ (2016)
  • ‘ይሖዋ ሆይ፣ ታውቀኛለህ’
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2011
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2014
w14 8/1 ገጽ 5

የሽፋኑ ርዕሰ ጉዳይ | አምላክ ስለ አንተ ያስባል?

አምላክ ስሜትህን ይረዳልሃል

“[“ይሖዋ፣” NW] ሆይ፤ መረመርኸኝ፤ ደግሞም ዐወቅኸኝ።”—መዝሙር 139:1

ዲ ኤን ኤ እና ሽል

“ዐይኖችህ ገና ያልተበጀውን አካሌን አዩ።”—መዝሙር 139:16

አንዳንዶች የሚጠራጠሩበት ምክንያት፦ ብዙዎች አምላክ የሰው ልጆችን የሚያየው እንደ ኃጢአተኞች ማለትም እንደረከሱና የእሱን ትኩረት ለማግኘት እንደማይበቁ አድርጎ እንደሆነ ይሰማቸዋል። በመንፈስ ጭንቀት ትሠቃይ የነበረችው ኬንድራ የአምላክን መሥፈርቶች ፍጹም በሆነ ሁኔታ ማሟላት ስላልቻለች በጥፋተኝነት ስሜት ተውጣ ነበር። በዚህም የተነሳ “መጸለይ አቁሜ ነበር” ብላለች።

የአምላክ ቃል ምን ያስተምራል? ይሖዋ ትኩረት የሚያደርገው በውስጣዊ ማንነትህ ላይ እንጂ ፍጹም ባለመሆንህ ላይ አይደለም። “እርሱ አፈጣጠራችንን ያውቃልና፤ ትቢያ መሆናችንንም ያስባል” በማለት መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል። ከዚህም በላይ እኛን የሚይዘን “እንደ ኃጢአታችን” አይደለም፤ ንስሐ ስንገባም በምሕረት ይቅር ይለናል።—መዝሙር 103:10, 14

ከእነዚህ ተከታታይ ርዕሶች በመጀመሪያው ላይ የተጠቀሰውን የእስራኤል ንጉሥ የነበረውን ዳዊትን እንውሰድ። ዳዊት ለአምላክ ባቀረበው ጸሎት ላይ እንዲህ ብሏል፦ “ዐይኖችህ ገና ያልተበጀውን አካሌን አዩ፤ . . . ገና አንዳቸው ወደ መኖር ሳይመጡ፣ በመጽሐፍ ተመዘገቡ። . . . እግዚአብሔር ሆይ፤ መርምረኝ፤ ልቤንም ዕወቅ።” (መዝሙር 139:16, 23) አዎን፣ ዳዊት ከባድ ኃጢአት የሠራበት ጊዜ ቢኖርም ከተጸጸተ ይሖዋ የልቡን ሁኔታ መመልከት እንደሚችል እርግጠኛ ነበር።

ይሖዋ ከማንም ሰው በላይ ጠንቅቆ ያውቅሃል። መጽሐፍ ቅዱስ “ሰው የውጭውን ገጽታ ያያል፤ እግዚአብሔር ግን ልብን ያያል” ይላል። (1 ሳሙኤል 16:7) አምላክ በዘር የወረስከው ነገር፣ አስተዳደግህ፣ አካባቢህና የራስህ ባሕርይ አንድ ላይ ተዳምረው አንተነትህን እንዴት እንደቀረጹት ያውቃል። ስህተት ብትሠራም እንኳ ምን ዓይነት ሰው ለመሆን ጥረት እያደረግህ እንዳለህ ይመለከታል፤ እንዲሁም ጥረትህን ከፍ አድርጎ ያየዋል።

ይሁንና አምላክ ስለ አንተ እውነተኛ ማንነት ያለውን ጥልቅ እውቀት አንተን ለማጽናናት የሚጠቀምበት እንዴት ነው?

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ