የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 10/94 ገጽ 8
  • ፍላጎት ያሳዩትን በፍቅር እርዷቸው

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ፍላጎት ያሳዩትን በፍቅር እርዷቸው
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—1994
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ፍላጎት ያሳዩትን ሁሉ ተከታትሎ በመርዳት እንዲጠቀሙ ማድረግ
    የመንግሥት አገልግሎታችን—1995
  • ፍላጎት ላላቸው ሁሉ ልባዊ አሳቢነት አሳዩ
    የመንግሥት አገልግሎታችን—1997
  • ዓላማ ያላቸው ተመላልሶ መጠየቆች
    የመንግሥት አገልግሎታችን—1995
  • ፍላጎት ላሳዩ ሰዎች ክትትል ማድረግ
    የመንግሥት አገልግሎታችን—1995
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—1994
km 10/94 ገጽ 8

ፍላጎት ያሳዩትን በፍቅር እርዷቸው

1 የይሖዋ መልአክ ደቀ መዝሙሩ ፊልጶስን ለአምላክ ቃል እውነት ልባዊ ፍላጎት ወዳሳየ ኢትዮጵያዊ ሲመራው ፊልጶስ ሰውዬው የሚያነበውን እንዲገባው ፍቅራዊ እርዳታ አድርጎለታል። (ሥራ 8:26–39) ፍላጎት ያሳዩትን ለመርዳት ተጨማሪ ጥረት እናደርጋለንን? መለኮታዊ ተልእኮአችን ደቀ መዛሙርት ማድረግንም የሚጨምር ስለሆነ ይህን ማድረግ አለብን። (ማቴ. 28:19, 20) እነሱን ለመርዳት ምን ማድረግ እንችላለን?

2 በየሳምንቱ ተመላልሶ መጠየቅ ለማድረግ ጊዜ መድብ። ፍላጎት ያሳዩትን ለመጠየቅ ዝግጅት አድርግ፤ በመጀመሪያ ጉብኝትህ የተጀመረውን ውይይት ለመቀጠል ሞክር። የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የመጀመርን ግብ በአእምሮህ ያዝ። በቅርብ ጊዜ የወጡ የመጠበቂያ ግንብ እና የንቁ! እትሞችን ለማበርከት ዘወትር ተመላልሰህ ሂድ። ሰውዬው ልባዊ ፍላጎት ካሳየ ኮንትራት እንዲገባ ልትጠይቀው ትችላለህ።

3 በመጀመሪያ ጉብኝትህ ወቅት ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ጥቅም አወያይተኸው ከነበረ “ማመራመር ” (ሪዝኒንግ) ከተባለው መጽሐፍ ገጽ 66 ላይ ባለው ሐሳብ ተጠቅመህ ውይይትህን ልትቀጥልና እንዲህ ልትል ትችላለህ:-

◼ “አንዳንዶች የመጽሐፍ ቅዱስ ምክር ለዘመናዊው ዓለም ተግባራዊ ጥቅም እንደሌለው ይሰማቸዋል። እርስዎስ ስለዚህ ጉዳይ ምን ይሰማዎታል? [መልስ እንዲሰጥ እድል ስጠው።] ደስተኛ የቤተሰብ ሕይወት እንዲኖረን የሚያስችል ጥሩ ምክር የሚሰጥ መጽሐፍ ተግባራዊ ጥቅም አለው ቢባል አይስማሙምን? [አስተያየት እንዲሰጥ ፍቀድለት።] የቤተሰብን ሕይወት የሚመለከቱ ንድፈ ሐሳቦችና ልማዶች ተለዋውጠዋል። እነሱ ያስከተሏቸው ዛሬ የምናያቸው ውጤቶች ጥሩ አይደሉም። ይሁን እንጂ መጽሐፍ ቅዱስ የሚለውን የሚሠሩበት ቤተሰቦች ጽኑና ደስተኛ ቤተሰብ ናቸው።” ቆላስይስ 3:18–21⁠ን አንብብ። መጽሐፍ ቅዱስን ማመን የሚችሉት ለምንድን ነው? የተባለውን ትራክት አበርክት፤ መጽሐፍ ቅዱስን በነፃ እንደምናስጠና ግለጽ።

4 ስለ ሙታን ሁኔታ በዚህ መልኩ ውይይት ልትጀምር ትችላለህ:-

◼ “ስለ ሙታን ሁኔታ ብዙ ይወራል። ስንሞት ምን እንሆናለን ብለው ያስባሉ? [መልስ አንዲሰጥ እድል ስጠው።] ብዙ ሃይማኖቶች ሕይወታችን በሆነ መንገድ ይቀጥላል በማለት ያስተምራሉ። ብዙዎች መጽሐፍ ቅዱስ ስለዚህ ጉዳይ የሚናገረውን ሲያውቁ ተገርመዋል። [መክብብ 9:5⁠ን አንብብ።] ሙታን አንዳች የማያውቁ ቢሆንም አልተረሱም። አምላክ በንጉሣዊ አገዛዙ ሥር እነሱን ወደ ሕይወት ለመመለስ ቃል ገብቷል።” የጥቅምት 15, 1994 መጠበቂያ ግንብ ን ወይም ለዘላለም መኖር የተባለውን መጽሐፍ ገጽ 162⁠ን ግለጥና ጥቅሶቹንና ሥዕሎቹን አብራራ። የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ማስጀመርን ግብ በማድረግ ሌላ ተመላልሶ መጠየቅ ለማድረግ ቀጠሮ ያዝ።

5 በዓለም ሁኔታዎች ላይ ወይም በሰዎች መካከል ስላለው አለመግባባት አስተያየት መስጠት ከፈለግህ እንዲህ ልትል ትችላለህ:-

◼ “አንዳንዶች አለመግባባትን መፍቻው መንገድ ውጊያ ብቻ ይመስላቸዋል። ስለዚህ ነገር ምን ይሰማዎታል? [መልስ እንዲሰጥ ፍቀድለት።] መጽሐፍ ቅዱስ አምላክ ሰዎች በአንድነት ሆነው በሰላም አንዲኖሩ እንደሚፈልግ ያሳያል። [ሮሜ 12:17, 18⁠ን አንብብ።] ይህ በአምላክ መንግሥት አማካይነት በዓለም አቀፍ ደረጃ እውን ይሆናል።” አምላክ ስለ እኛ በእርግጥ ያስባልን? በተባለው ብሮሹር ገጽ 25, 26⁠ን አሳየው። ኢየሱስ ‘የአምላክ ፍቃድ በሰማይ እንደሆነ እንዲሁም በምድር ይሁን’ ብለን እንድንጸልይ ለምን እንዳስተማረን ለመግለጽ ተመልሰህ መምጣት አንደምትፈልግ ተናገር።— ማቴ. 6:10

6 ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ የሚመራው ሳይኖር የሚያነበውን መረዳት እንደማይችል አምኗል። (ሥራ 8:31) ፊልጶስ የሚያስፈልገውን እርዳታ በፍቅር ሰጥቶታል። እኛም በተመሳሳይ መንገድ ሌሎችን በመርዳት ለእነሱ ያለንን እውነተኛ ፍቅር ልናሳይ እንችላለን።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ