የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 7/00 ገጽ 1
  • “ዝም ማለት አንችልም”

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • “ዝም ማለት አንችልም”
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2000
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የአምላክን ቃል በድፍረት መናገርህን ቀጥል
    እውነተኛውን አንድ አምላክ አምልክ
  • የአምላክን ቃል በድፍረት መናገርህን ቀጥል
    እውነተኛው አንድ አምላክ ያስገኘው የአምልኮ አንድነት
  • ‘የአምላክን ቃል በድፍረት ተናገሩ’
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2010
  • “አምላክን እንደ ገዢያችን አድርገን ልንታዘዝ ይገባል”
    ‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—2000
km 7/00 ገጽ 1

“ ዝም ማለት አንችልም”

1 ኢየሱስ ክርስቶስ የስብከቱን ሥራ በቅርብ ሆኖ እየተከታተለው ነው። (ማቴ. 28:​20፤ ማር. 13:​10) ወደ ስድስት ሚልዮን የሚጠጉት ንቁ የመንግሥቱ አዋጅ ነጋሪዎች በ234 አገሮች ውስጥ ምሥክርነት እየሰጡ ቢሆንም ሥራው ተጠናቋል ብለን ማሰብ አይኖርብንም። አምላክ በቃ ብሎ ሥራውን እስከሚያስቆምበት ጊዜ ድረስ ስለተማርናቸው ነገሮች “ከመናገር ዝም ማለት አንችልም።”​—⁠ሥራ 4:​20

2 በአምላክ መንፈስ ተማመኑ:- ሰይጣን ከባድ ተጽእኖ በማድረስ እኛን ተስፋ ለማስቆረጥ ይሞክራል። (ራእይ 12:​17) ፍጹም ያልሆነው ሥጋችንም ብዙ ችግር ይፈጥርብናል። እንዲህ ያሉት ነገሮች በጣም አስፈላጊ ከሆነው የስብከት ሥራ በቀላሉ ትኩረታችንን ሊወስዱት ቢችሉም በይሖዋ ከታመንን መንፈሱ ማንኛውንም መሰናክል እንድንወጣ ይረዳናል።

3 የመጀመሪያው መቶ ዘመን የክርስቲያን ጉባኤ ከባድ ስደት በደረሰበት ጊዜ ወንድሞች ቃሉን በድፍረት መናገራቸውን እንዲቀጥሉ አምላክ እንዲረዳቸው ጸልየዋል። ይሖዋም መንፈሱን በላያቸው በማፍሰስ እንዲሁም በስብከቱ ሥራ ለመቀጠል የሚያስፈልጋቸውን ቅንዓት እንዲያሳዩና ቁርጥ አቋም እንዲይዙ በመርዳት ለጸሎታቸው መልስ በመስጠቱ ወንድሞች ምሥራቹን ያለማቋረጥ በድፍረት ማወጃቸውን ቀጥለዋል።​—⁠ሥራ 4:​29, 31፤ 5:​42

4 የሰዎችን ትችት አትፍሩ:- ሰዎች የሚሰጡት አስተያየት ወይም የሚካሄድብን ስም የማጥፋት ዘመቻ እንድንፈራ ያደርገን ይሆናል። ሆኖም ጴጥሮስና ሌሎቹ ሐዋርያት ለአይሁድ የፍርድ ሸንጎ በድፍረት የተናገሩትን በሥራ 5:​29-32 ላይ ተመዝግቦ የሚገኘውን ታሪክ አስታውሱ። የሕግ መምህር የሆነው ገማልያል እንደተናገረው የአምላክ ሥራ ሊጨናገፍ አይችልም። በእኛ ኃይል የሚሠራ ሥራ አይደለም። ይህ ታላቅ ሥራ የአምላክ ድጋፍ ያለውና እርሱ ብቻ ሊፈጽመው የሚችለው ሥራ ነው!​—⁠ዘካ. 4:​6

5 ምሥራቹን በቅንዓት እንድናውጅ የሚረዳንን መንፈሱን እንዲሰጠን ይሖዋን ዘወትር እንለምን። እኛም እንደ ኤርምያስ የመንግሥቱ መልእክት በአጥንቶቻችን ውስጥ እንደ ገባ እንደሚነድድ እሳት ነው ለማለት እንችል ዘንድ ምኞታችን ነው። (ኤር. 20:​9) ዝም ማለት አንችልም!

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ