ግንቦት 10 የሚጀምር ሳምንት
ግንቦት 10 የሚጀምር ሳምንት
□ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
lv ምዕ. 13 አን. 1-4፤ በገጽ 148-149, 158-159 የሚገኙት ሣጥኖች
□ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ 2 ሳሙኤል 4-8
ቁ. 1፦ 2 ሳሙኤል 6:1-13
ቁ. 2፦ ስለ ቫለንታይን ቀን፣ ስለ እናቶች ቀንና ብሔራዊ ስሜት ስለሚንጸባረቅባቸው ክብረ በዓላት ምን የምናውቀው ነገር አለ? (rs ከገጽ 182 አን. 3 እስከ ገጽ 183 አን. 2)
ቁ. 3፦ ስግብግብነት ጣኦት አምልኮ እንደሆነ ተደርጎ የተገለጸው ለምንድን ነው? (ኤፌ. 5:5)
□ የአገልግሎት ስብሰባ፦
5 ደቂቃ፦ ማስታወቂያዎች።
10 ደቂቃ፦ በክልላችሁ ውስጥ ለሚገኙ ሰዎች እርዳታ ስጡ። በአገልግሎት ትምህርት ቤት መጽሐፍ ከገጽ 188 አን. 4 እስከ ገጽ 189 መጨረሻ ድረስ ባሉት ሐሳቦች ላይ ተመሥርቶ ከአድማጮች ጋር በሚደረግ ውይይት የሚቀርብ። ሌሎች ሰዎች ልባዊ አሳቢነት ስላሳዩት እድገት ማድረግ ለቻለ አንድ አስፋፊ አጭር ቃለ ምልልስ አድርግ።
10 ደቂቃ፦ ንጹሕ የመንግሥት አዳራሽ ለይሖዋ ክብር ያመጣል። በሽማግሌ የሚቀርብ ንግግር። ይሖዋ ቅዱስ አምላክ ነው፤ በመሆኑም ሕዝቦቹ ለአካላዊ ንጽሕናቸው ቅድሚያ መስጠት ይገባቸዋል። (ዘፀ. 30:17-21፤ 40:30-32) የአምልኮ ቦታችንን በንጽሕና በመያዝና አስፈላጊውን ጥገና በማድረግ ለይሖዋ ክብር እናመጣለን። (1 ጴጥ. 2:12) የመንግሥት አዳራሹን ጽዳትና ጥገና ለሚያስተባብረው ወንድም ጉባኤው ይህን በሚመለከት ስላደረገው ዝግጅት ቃለ ምልልስ አድርግለት። አንድ የመንግሥት አዳራሽ በጥሩ ሁኔታ የተያዘ መሆኑ በአካባቢው ለሚኖሩ ሰዎች ምሥክርነት የሚሰጠው እንዴት እንደሆነ የሚያሳይ ከጉባኤያችሁ ወይም ከጽሑፍ ላይ የተገኘ ተሞክሮ ተናገር። ሁሉም የመንግሥት አዳራሹን በሚገባ በመያዙ ሥራ እንዲካፈሉ አበረታታ።
10 ደቂቃ፦ “ይህ የመንግሥት ምሥራች ይሰበካል!” በጥያቄና መልስ የሚቀርብ።