ጥቅምት 8 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
ጥቅምት 8 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 28 እና ጸሎት
□ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
fy ምዕ. 16 ከአን. 1-7 (30 ደቂቃ)
□ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ ዳንኤል 7-9 (10 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ ዳንኤል 7:13-22 (4 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ እውነተኛ ክርስቲያኖች የተደራጁ እንደሚሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ ያሳያል?—rs ገጽ 282 ከአን. 1-4 (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ ይሖዋ ታማኝ የሆነው በየትኞቹ መንገዶች ነው?—ራእይ 15:4፤ 16:5 (5 ደቂቃ)
□ የአገልግሎት ስብሰባ፦
10 ደቂቃ፦ አንድ ሰው እንዲህ ቢልስ፦ ‘ሥራ አለብኝ።’ በማመራመር መጽሐፍ ከገጽ 19 አንቀጽ 7 እስከ ገጽ 20 አንቀጽ 5 ባለው ሐሳብ ላይ ተመሥርቶ በውይይት የሚቀርብ። በመጽሐፉ ላይ በተሰጡት አንዳንድ መልሶች እንዲሁም በክልላችሁ ውስጥ ውጤታማ በሆኑ ሌሎች ምላሾች ላይ ተወያዩ። ሁለት አጠር ያሉ ሠርቶ ማሳያዎች እንዲቀርቡ አድርግ።
10 ደቂቃ፦ ምን ትምህርት እናገኛለን? በውይይት የሚቀርብ። ማቴዎስ 21:12-16 እና ሉቃስ 21:1-4 እንዲነበቡ አድርግ። ከዚያም ከእነዚህ ዘገባዎች በምናገኘው ትምህርት ላይ ተወያዩ።
10 ደቂቃ፦ “በምሽት አገልግሎት መካፈል ትችላላችሁ?” በጥያቄና መልስ የሚቀርብ። በአንቀጽ 2 ላይ ስትወያዩ አድማጮች በምሽት አገልግሎት ሲካፈሉ ያገኟቸውን አንዳንድ ተሞክሮዎች እንዲናገሩ ጋብዝ።
መዝሙር 47 እና ጸሎት