የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • sjj መዝ. 146
  • ‘ሁሉንም ነገር አዲስ ያደርጋል’

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ‘ሁሉንም ነገር አዲስ ያደርጋል’
  • ለይሖዋ ‘በደስታ ዘምሩ’
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ሁሉንም ነገር አዲስ ያደርጋል
    ለይሖዋ ዘምሩ
  • ይሖዋ ንጉሣችን ነው!
    ለይሖዋ ‘በደስታ ዘምሩ’
  • ይሖዋ ንጉሣችን ነው!
    ለይሖዋ ዘምሩ
  • “የመጨረሻው ጠላት” ድል ይደረጋል!
    መጠበቂያ ግንብ—1993
ለተጨማሪ መረጃ
ለይሖዋ ‘በደስታ ዘምሩ’
sjj መዝ. 146

መዝሙር 146

‘ሁሉንም ነገር አዲስ ያደርጋል’

በወረቀት የሚታተመው

(ራእይ 21:1-5)

  1. 1. የአምላክ መንግሥት መግዛቱን ጀምሯል።

    የይሖዋ ልጅ ሥልጣኑን ይዟል።

    ከሰማይ ላይ ሰይጣንን አባሯል፤

    በምድርም ያምላክ ፈቃድ ይሆናል።

    (አዝማች)

    ተስፋው እንዴት ያስደስታል!

    አምላክ ከሰዎች ጋር ያድራል።

    ሐዘን፣ ሥቃይ አይኖርም ጨርሶ፤

    ይወገዳል ሞት፣ እንባና ለቅሶ።

    ‘ሁሉን አዲስ አደርጋለሁ’ ብሏል፤

    እውነት ነው፤ ይፈጸማል።

  2. 2. አዲሷን ’የሩሳሌም ይዩ ሰዎች፤

    የበጉ ሙሽራ ተውባለች።

    የከበረ ዕንቁ ሰጣት ድምቀት፤

    ይሖዋ አምላክ ሆነላት መብራት።

    (አዝማች)

    ተስፋው እንዴት ያስደስታል!

    አምላክ ከሰዎች ጋር ያድራል።

    ሐዘን፣ ሥቃይ አይኖርም ጨርሶ፤

    ይወገዳል ሞት፣ እንባና ለቅሶ።

    ‘ሁሉን አዲስ አደርጋለሁ’ ብሏል፤

    እውነት ነው፤ ይፈጸማል።

  3. 3. በሮቿ የማይዘጉ ቀን ከሌት፤

    ይቺ ከተማ የሰው ልጅ ሐሴት።

    ከሷ በሚፈነጥቀው ብርሃን፣

    ሕዝቦች ይጓዙ አይተው ጸዳሏን።

    (አዝማች)

    ተስፋው እንዴት ያስደስታል!

    አምላክ ከሰዎች ጋር ያድራል።

    ሐዘን፣ ሥቃይ አይኖርም ጨርሶ፤

    ይወገዳል ሞት፣ እንባና ለቅሶ።

    ‘ሁሉን አዲስ አደርጋለሁ’ ብሏል፤

    እውነት ነው፤ ይፈጸማል።

(በተጨማሪም ማቴ. 16:3⁠ን፣ ራእይ 12:7-9⁠ን እና 21:23-25⁠ን ተመልከት።)

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ