የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 9/05 ገጽ 11
  • አዲስ የወረዳ ስብሰባ ፕሮግራም

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • አዲስ የወረዳ ስብሰባ ፕሮግራም
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2005
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ከተጠመቃችሁ በኋላም “አዲሱን ስብዕና” መልበሳችሁን ቀጥሉ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2022
  • የወረዳ ስብሰባ ክለሳ
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2005
  • አዲስ የወረዳ ስብሰባ ፕሮግራም
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2004
  • ለክርስቲያን አገልጋዮች የተደረገ ዝግጅት
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2010
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—2005
km 9/05 ገጽ 11

አዲስ የወረዳ ስብሰባ ፕሮግራም

በዚህ ብልሹና አሮጌ ሥርዓት የመደምደሚያ ቀኖች ውስጥ ስንኖር መንፈሳዊ ልብሳችንን እንዲሁም ክርስቲያናዊ መለያችንን ጠብቀን መኖራችን በጣም አስፈላጊ ነው። (ራእይ 16:15) ስለሆነም የ2006 የአገልግሎት ዓመት የወረዳ ስብሰባ “አዲሱን ሰው ልበሱ” የሚል ጭብጥ ያለው መሆኑ ተገቢ ነው።—ቈላ. 3:10

የመጀመሪያው ቀን:- በስብሰባው ላይ ከሚቀርቡት ተከታታይ ንግግሮች መካከል የመጀመሪያው “የአዲሱን ሰው የተለያዩ ገጽታዎች ማንጸባረቅ” የሚል ጭብጥ ያለው ሲሆን አዲሱን ሰው መልበሳችን በሁሉም የኑሮ ዘርፎች እንዴት እንደሚጠቅመን ያጎላል። አዲሱን ሰው መልበስ የምንችለው እንዴት ነው? “በተገቢው ሁኔታ ለማሰላሰል ራሳችሁን ገሥጹ” እና “አዲሱን ሰው ለመቅረጽ የሚረዳ ትምህርት” በሚል ጭብጥ ከሚቀርቡት የዕለቱ የመደምደሚያ ንግግሮች የዚህን ጥያቄ መልስ እናገኛለን።

ሁለተኛው ቀን:- “የጠቢብ አንደበት ይኑራችሁ” የሚል ጭብጥ ባለው በሁለተኛው ተከታታይ ንግግር ላይ አዲሱን ሰው መልበሳችን በአንደበት አጠቃቀማችን ላይ ምን ተጽዕኖ እንደሚኖረው ይብራራል። የሕዝብ ንግግሩ ጭብጥ “ክፉውን እያሸነፋችሁት ነው?” የሚል ሲሆን በሰይጣን ዘዴዎች እንዳንታለል ነቅቶ የመኖርን አስፈላጊነት ጎላ አድርጎ ይገልጻል። በስብሰባው ማጠቃለያ ላይ የሚቀርቡት ሁለት ንግግሮች “ከዓለም ርኩሰት ራሳችሁን ጠብቁ” እንዲሁም “ውስጣዊ ሰውነታችን በየዕለቱ ይታደስ” የሚል ጭብጥ ያላቸው ሲሆን የይሖዋን የጽድቅ መንገድ ከሚቃረን አመለካከትና አኗኗር በመራቅ እርሱን በማምለክ ጸንተን እንድንኖር ይረዱናል።

አዲሱን ሰው እንድንለብስና ጠብቀን እንድንኖር የሚሰጠንን እንዲህ ዓይነቱን ግሩም ማበረታቻ በጉጉት እንጠብቃለን!

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ