የልዩ ስብሰባ ቀን ክለሳ
ይህ ክፍል በ2006 የአገልግሎት ዓመት በሚካሄደው የልዩ ስብሰባ ፕሮግራም ላይ የሚቀርበውን ትምህርት ለመከለስ የተዘጋጀ ሲሆን ስብሰባው ከመካሄዱ ትንሽ ቀደም ብሎና ከተካሄደ ከጥቂት ጊዜ በኋላ በአገልግሎት ስብሰባ ላይ ይቀርባል። ሰብሳቢ የበላይ ተመልካቹ ከስብሰባው በፊትም ሆነ ስብሰባው ተደርጎ የተወሰኑ ጊዜያት ካለፉ በኋላ በመስከረም 2004 የመንግሥት አገልግሎታችን ገጽ 1 ላይ ያለውን መመሪያ ተከትሎ ክለሳው እንዲቀርብ ያደርጋል። በክለሳው ወቅት ሁሉም ጥያቄዎች መጠየቅ ያለባቸው ሲሆን ክለሳው በስብሰባው ላይ የቀረበውን ትምህርት እንዴት በሥራ ላይ ማዋል እንደምንችል የሚያጎላ መሆን አለበት።
የጠዋት ክፍለ ጊዜ
1. ጤናማ ዓይን መያዝ ሲባል ምን ማለት ነው? በዛሬው ጊዜ እንዲህ ማድረጉ ከባድ የሚሆነውስ ለምንድን ነው? (“ጤናማ ዓይን ሊኖራችሁ የሚገባው ለምንድን ነው?”)
2. ጤናማ ዓይን መያዝ ምን ጥቅሞች ያስገኝልናል? (“ጤናማ ዓይን በመያዝ በረከት እጨዱ”)
3. የተለመዱ ናቸው የሚባሉ አንዳንድ እንቅስቃሴዎች ምን አደጋ አላቸው? (“ክፉ በሆነ ዓለም ውስጥ ጤናማ ዓይን መያዝ”)
የከሰዓት በኋላ ክፍለ ጊዜ
4. ወላጆችም ሆኑ ሌሎች ወንድሞች፣ ወጣቶች መንፈሳዊ ግቦችን እንዲከታተሉ መርዳት የሚችሉት እንዴት ነው? (“ፍላጾቻቸውን አስተካክለው የሚያነጣጥሩ ወላጆች” እና “መንፈሳዊ ግቦች ላይ ለመድረስ የሚጣጣሩ ወጣቶች”)
5. (ሀ) በግለሰብ (ለ) በቤተሰብ (ሐ) በጉባኤ ደረጃ ከይሖዋ ድርጅት ጋር ወደፊት መጓዝ የምንችለው እንዴት ነው? (“ትኩረታችሁ ሳይከፋፈል ከይሖዋ ድርጅት ጋር እኩል ተራመዱ”)