የአቀራረብ ናሙናዎች
በወሩ የመጀመሪያ ቅዳሜ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ለማስጀመር የሚረዳ አቀራረብ
“ከጎረቤቶቻችን ጋር አጠር ያለ ውይይት እያደረግን ነው። ከሚያጋጥሙን በጣም ከባድ ችግሮች መካከል አንዱ ምን እንደሆነ ከሰዎች ጋር አንስተን ስንወያይ ብዙዎች የጠቀሱት፣ የሚወዱትን ሰው በሞት ማጣት ነው። እርስዎስ እንደዚያ ይሰማዎታል?” [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] ይህን ሐሳብ የሚያበረታታ ሆኖ አግኝቼዋለሁ።” የጥቅምት 1ን መጠበቂያ ግንብ ስጠውና በመጨረሻ ገጽ ላይ ያለውን ዓምድ አሳየው። ከዚያም በመጀመሪያው ጥያቄ ሥር ባለው ሐሳብ ላይ እና በዚያ ውስጥ ከተጠቀሱት ጥቅሶች መካከል ቢያንስ በአንዱ ላይ ተወያዩ። መጽሔቶቹን ካበረከትክለት በኋላ በሚቀጥለው ጥያቄ ላይ ለመወያየት ቀጠሮ ያዝ።
መጠበቂያ ግንብ ጥቅምት 1
“ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስ እንዲያነብቡ እያበረታታን ነው። አንዳንዶች ለመጽሐፍ ቅዱስ ፍላጎት ባይኖራቸውም ብዙ ሰዎች ለመጽሐፍ ቅዱስ ትልቅ ቦታ ይሰጣሉ። እርስዎ በዚህ ጉዳይ ላይ ምን አመለካከት አለዎት? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] መጽሐፍ ቅዱስ ምን እንደሚል ላሳይዎት። [1 ተሰሎንቄ 2:13ን አንብብ።] መቼም መጽሐፍ ቅዱስ የአምላክ ቃል ከሆነ ልናነብበው ይገባል በሚለው ሐሳብ እንደሚስማሙ እርግጠኛ ነኝ። ይህ መጽሔት፣ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ምን እንደሚናገርና ልናነብበው የሚገባው ለምን እንደሆነ በአጭሩ ያብራራል።”
ንቁ! ጥቅምት
“አንድ ጥያቄ ባቀርብልዎ ደስ ይለኛል፦ ብዙ ንብረት ባይኖረንም እንኳ ባለን ነገር ረክተን መኖር እንችላለን? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] መጽሐፍ ቅዱስ ምን እንደሚል ላሳይዎት። [1 ጢሞቴዎስ 6:8ን አንብብ።] ይህ መጽሔት ለቁሳዊ ነገሮች ሚዛናዊ አመለካከት እንዲኖረን ያበረታታል፤ በተጨማሪም ገንዘብ ሊገዛቸው የማይችላቸውን ሦስት ውድ ነገሮች ይዘረዝራል።”