የአቀራረብ ናሙናዎች
መጠበቂያ ግንብ ታኅሣሥ 1
“መጽሐፍ ቅዱስን በተመለከተ በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነት ያገኘ አንድ የተሳሳተ አመለካከት አለ። ብዙ ሰዎች ለመጽሐፍ ቅዱስ አክብሮት ቢኖራቸውም ለመረዳት የሚከብድ መጽሐፍ እንደሆነ ይሰማቸዋል። እርስዎስ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ዓይነት መጽሐፍ እንደሆነ ይሰማዎታል? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] መጽሐፍ ቅዱስን ለመረዳት ጥረት ማድረጋችን አስፈላጊ የሆነበትን አንድ ምክንያት ላሳይዎት። [ሮም 15:4ን አንብብ።] ይህ መጽሔት፣ መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው ልንረዳው በምንችል መንገድ ነው የምንለው ለምን እንደሆነ ያብራራል። በተጨማሪም መጽሐፍ ቅዱስን ለመረዳት የሚያስችሉ አንዳንድ ጠቃሚ ነጥቦችን ይዟል።”
ንቁ! ታኅሣሥ
“ዛሬ የመጣነው ቤተሰብን በተመለከተ አንዳንድ ሐሳቦችን ልንነግርዎት ነው። በቤቱ ውስጥ ሰላምና ስምምነት እንዲኖር የማይፈልግ ሰው የለም። ይሁንና በቤተሰብ ውስጥ ጨርሶ አለመግባባት እንዳይፈጠር ማድረግ የሚቻል ይመስልዎታል? ታዲያ አለመግባባት ሲፈጠር ሁኔታውን መፍታት የሚቻልበትን መንገድ መማር የምንችለው እንዴት ነው? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የሚገኝ አንድ ምሳሌ ምን እንደሚል ላንብብልዎት። [ምሳሌ 26:20ን አንብብ።] ይህ መጽሔት፣ ሰዎች የቤተሰብ ሕይወታቸው ይበልጥ ሰላም የሰፈነበት እንዲሆን የሚረዱ ጠቃሚ ምክሮችን ይዟል።”