የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • mwb16 መጋቢት ገጽ 2
  • እንግዶቻችንን መቀበል

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • እንግዶቻችንን መቀበል
  • ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ (2016)
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ሞቅ ያለ አቀባበል አድርጉላቸው!
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2013
  • ትልቅ ምሥክርነት ይሰጣል
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2011
  • በመታሰቢያው በዓል ላይ የሚገኙትን ሰዎች እንዴት መርዳት እንችላለን?
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2008
  • በመታሰቢያው በዓል ላይ ጥሩ አቀባበል አድርጉላቸው
    የመንግሥት አገልግሎታችን—1994
ለተጨማሪ መረጃ
ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ (2016)
mwb16 መጋቢት ገጽ 2

ክርስቲያናዊ ሕይወት

እንግዶቻችንን መቀበል

መጋቢት 23 ከ12 ሚሊዮን የሚበልጡ እንግዶች በመታሰቢያው በዓል ይገኛሉ ተብሎ ይገመታል። ንግግር የሚያቀርበው ወንድም ይሖዋ ስላዘጋጀልን ቤዛ እንዲሁም በቤዛው ምክንያት የሰው ልጆች ስለሚያገኟቸው አንዳንድ በረከቶች ስለሚጠቅስ ለእነዚህ ሰዎች አስደናቂ ምሥክርነት ይሰጣል። (ኢሳ 11:6-9፤ 35:5, 6፤ 65:21-23፤ ዮሐ 3:16) ይሁንና በዚህ ለየት ያለ ዝግጅት ላይ ምሥክርነት የሚሰጠው ተናጋሪው ብቻ አይደለም። ሁላችንም እንግዶቻችንን ሞቅ ባለ ስሜት በመቀበል ግሩም ምሥክርነት መስጠት እንችላለን። (ሮም 15:7) ይህን ለማድረግ የሚረዱ አንዳንድ ሐሳቦች ቀጥሎ ቀርበዋል።

አንድ የይሖዋ ምሥክር ለመታሰቢያው በዓል የመጣን እንግዳ ሲቀበል፤ አንድ የይሖዋ ምሥክር በመታሰቢያው በዓል ላይ የተጋበዘ ሰው የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችን እንዲከታተል ሲረዳው
  • ቦታችን ላይ ተቀምጠን ፕሮግራሙ እስኪጀምር ከመጠበቅ ይልቅ እንግዶችንና የቀዘቀዙ አስፋፊዎችን በፈገግታ እንቀበል፤ እንዲሁም ለእነሱ ሞቅ ያለ ሰላምታ እንስጣቸው

  • ጋብዘናቸው ለመጡት የምናውቃቸው ሰዎች ለየት ያለ ትኩረት መስጠት ያለብን ቢሆንም መጋበዣው ደርሷቸው የመጡትንም ለመርዳት ንቁ መሆን አለብን። አዳዲሶች አብረዋችሁ እንዲቀመጡ ጋብዟቸው። መጽሐፍ ቅዱስና መዝሙር መጽሐፍ አብረዋችሁ እንዲከታተሉ አድርጉ

  • ስብሰባው ሲያልቅ ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት ዝግጁ ሁኑ። ከእናንተ በኋላ በዚያው አዳራሽ የመታሰቢያውን በዓል የሚያከብር ሌላ ጉባኤ ካለና አዳራሹን በፍጥነት መልቀቅ የሚጠበቅባችሁ ከሆነ በጥቂት ቀናት ውስጥ ተገናኝታችሁ ለመነጋገር ቀጠሮ ያዙ። አድራሻው ከሌላችሁ እንዲህ ልትሉት ትችላላችሁ፦ “በዓሉን እንዴት እንዳገኘኸው ብትነግረኝ ደስ ይለኛል። እንዴት መገናኘት እንችላለን?”

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ