መዝሙር 150
እገዛ የሚያስፈልጋቸውን መርዳት
በወረቀት የሚታተመው
አምላክ ያውቃል ’ሚበጀንን፣
ደስታ፣ ስኬት ’ሚሰጠንን።
ለማገልገል የሚያስችለን
ብዙ መንገድ ከፈተልን።
(አዝማች)
እገዛ ሲያስፈልግ
ሄደን እንርዳ።
ምርጣችንን እንስጥ፤ አለብን
የፍቅር ዕዳ።
ሁሉም አገር አለ ሥራ፤
ይፈለጋል የኛ ’ርዳታ።
አሳቢነት በማሳየት
እንችላለን ማገዝ፣ መርዳት።
(አዝማች)
እገዛ ሲያስፈልግ
ሄደን እንርዳ።
ምርጣችንን እንስጥ፤ አለብን
የፍቅር ዕዳ።
ባቅራቢያችን ባለ ቦታ
እንካፈል በግንባታ።
ለሰው ሁሉ ለመመሥከር
እንዲያስችለን ቋንቋ ’ንማር።
(አዝማች)
እገዛ ሲያስፈልግ
ሄደን እንርዳ።
ምርጣችንን እንስጥ፤ አለብን
የፍቅር ዕዳ።
(በተጨማሪም ዮሐ. 4:35ን፣ ሥራ 2:8ን እና ሮም 10:14ን ተመልከት።)