የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ኤርምያስ 22
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ኤርምያስ የመጽሐፉ ይዘት

      • በክፉ ነገሥታት ላይ የተላለፈ የፍርድ መልእክት (1-30)

        • ስለ ሻሉም የተነገረ ቃል (10-12)

        • ስለ ኢዮዓቄም የተነገረ ቃል (13-23)

        • ስለ ኮንያሁ የተነገረ ቃል (24-30)

ኤርምያስ 22:1

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ቤተ መንግሥት።”

ኤርምያስ 22:3

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ወላጅ አልባ የሆነውን ልጅ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘሌ 19:15፤ ኢሳ 1:17፤ ሕዝ 22:7፤ ሚክ 2:2
  • +2ነገ 24:3, 4፤ ኤር 7:6, 7

ኤርምያስ 22:4

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ነገ 2:12
  • +ኤር 17:24, 25

ኤርምያስ 22:5

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 39:8፤ ሚክ 3:12

ኤርምያስ 22:6

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 6:11፤ ኤር 7:34

ኤርምያስ 22:7

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “እቀድሳለሁ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሕዝ 9:1
  • +ኤር 21:14

ኤርምያስ 22:8

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 29:24-26፤ 1ነገ 9:8, 9፤ ሰቆ 2:15

ኤርምያስ 22:9

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 22:16, 17

ኤርምያስ 22:11

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ኢዮአካዝ ተብሎም ይጠራል።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 23:29, 30
  • +1ዜና 3:15፤ 2ዜና 36:1

ኤርምያስ 22:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 23:34፤ 2ዜና 36:4

ኤርምያስ 22:13

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘሌ 19:13፤ ሚክ 3:9, 10

ኤርምያስ 22:15

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 22:1, 2፤ 23:23, 25

ኤርምያስ 22:18

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 23:34፤ 2ዜና 36:4

ኤርምያስ 22:19

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 36:30
  • +2ዜና 36:5, 6

ኤርምያስ 22:20

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 32:49
  • +2ነገ 24:7

ኤርምያስ 22:21

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 2:31፤ 6:16
  • +ዘዳ 9:7፤ መሳ 2:11

ኤርምያስ 22:22

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 23:1፤ ሕዝ 34:2

ኤርምያስ 22:23

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “ምጥ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 22:6
  • +ኢሳ 2:12, 13
  • +ኤር 4:31፤ 6:24

ኤርምያስ 22:24

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ዮአኪን እና ኢኮንያን ተብሎም ይጠራል።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 23:34
  • +2ነገ 24:6፤ ኤር 22:28፤ 37:1፤ ማቴ 1:11

ኤርምያስ 22:25

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍስህን በሚሿት።”

  • *

    ቃል በቃል “በናቡከደረጾር።” ናቡከደነጾር የሚለው ስም የሚጻፍበት ሌላው መንገድ ነው።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 24:12, 15፤ 2ዜና 36:9, 10፤ ኤር 24:1፤ 29:1, 2

ኤርምያስ 22:27

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍሳቸውን ወደሚያነሱባት ምድር።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 52:31-34

ኤርምያስ 22:28

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ዜና 3:17, 18

ኤርምያስ 22:29

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “መሬት።”

ኤርምያስ 22:30

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “በቀኖቹ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ዜና 36:9, 10፤ ኤር 36:30፤ ማቴ 1:12

ተዛማጅ ሐሳብ

ኤር. 22:3ዘሌ 19:15፤ ኢሳ 1:17፤ ሕዝ 22:7፤ ሚክ 2:2
ኤር. 22:32ነገ 24:3, 4፤ ኤር 7:6, 7
ኤር. 22:41ነገ 2:12
ኤር. 22:4ኤር 17:24, 25
ኤር. 22:5ኤር 39:8፤ ሚክ 3:12
ኤር. 22:6ኢሳ 6:11፤ ኤር 7:34
ኤር. 22:7ሕዝ 9:1
ኤር. 22:7ኤር 21:14
ኤር. 22:8ዘዳ 29:24-26፤ 1ነገ 9:8, 9፤ ሰቆ 2:15
ኤር. 22:92ነገ 22:16, 17
ኤር. 22:112ነገ 23:29, 30
ኤር. 22:111ዜና 3:15፤ 2ዜና 36:1
ኤር. 22:122ነገ 23:34፤ 2ዜና 36:4
ኤር. 22:13ዘሌ 19:13፤ ሚክ 3:9, 10
ኤር. 22:152ነገ 22:1, 2፤ 23:23, 25
ኤር. 22:182ነገ 23:34፤ 2ዜና 36:4
ኤር. 22:19ኤር 36:30
ኤር. 22:192ዜና 36:5, 6
ኤር. 22:20ዘዳ 32:49
ኤር. 22:202ነገ 24:7
ኤር. 22:21ኤር 2:31፤ 6:16
ኤር. 22:21ዘዳ 9:7፤ መሳ 2:11
ኤር. 22:22ኤር 23:1፤ ሕዝ 34:2
ኤር. 22:23ኤር 22:6
ኤር. 22:23ኢሳ 2:12, 13
ኤር. 22:23ኤር 4:31፤ 6:24
ኤር. 22:242ነገ 23:34
ኤር. 22:242ነገ 24:6፤ ኤር 22:28፤ 37:1፤ ማቴ 1:11
ኤር. 22:252ነገ 24:12, 15፤ 2ዜና 36:9, 10፤ ኤር 24:1፤ 29:1, 2
ኤር. 22:27ኤር 52:31-34
ኤር. 22:281ዜና 3:17, 18
ኤር. 22:302ዜና 36:9, 10፤ ኤር 36:30፤ ማቴ 1:12
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
  • 23
  • 24
  • 25
  • 26
  • 27
  • 28
  • 29
  • 30
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ኤርምያስ 22:1-30

ኤርምያስ

22 ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ “ወደ ይሁዳ ንጉሥ ቤት* ወርደህ ይህን መልእክት ተናገር። 2 እንዲህ በል፦ ‘በዳዊት ዙፋን ላይ የተቀመጥከው የይሁዳ ንጉሥ ሆይ፣ አንተም ሆንክ አገልጋዮችህ እንዲሁም በእነዚህ በሮች የሚገባው ሕዝብህ የይሖዋን ቃል ስሙ። 3 ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ “ለፍትሕና ለጽድቅ ቁሙ። የተዘረፈውን ሰው ከአጭበርባሪው እጅ ታደጉ። ከባዕድ አገር የመጣውን ሰው አታንገላቱ፤ አባት የሌለውን ልጅ* ወይም መበለቲቱን አትበድሉ።+ በዚህም ስፍራ ንጹሕ ደም አታፍስሱ።+ 4 ይህን ቃል በሚገባ ብትጠብቁ፣ በዳዊት ዙፋን ላይ የሚቀመጡ ነገሥታት+ በሠረገሎችና በፈረሶች ላይ ተቀምጠው ከአገልጋዮቻቸውና ከሕዝቦቻቸው ጋር በዚህ ቤት በሮች ይገባሉ።”’+

5 “‘ይህን ቃል ባትታዘዙ ግን’ ይላል ይሖዋ፣ ‘ይህ ቤት እንደሚወድም በራሴ እምላለሁ።’+

6 “ይሖዋ የይሁዳን ንጉሥ ቤት አስመልክቶ እንዲህ ይላልና፦

‘አንተ ለእኔ እንደ ጊልያድና

እንደ ሊባኖስ ተራራ አናት ነህ።

ይሁንና ምድረ በዳ አደርግሃለሁ፤

ከተሞችህን በሙሉ ሰው አልባ አደርጋቸዋለሁ።+

 7 በአንተ ላይ ጥፋት የሚያደርሱ ሰዎችን፣

እያንዳንዳቸውን ከጦር መሣሪያዎቻቸው ጋር እሾማለሁ።*+

ምርጥ የሆኑ አርዘ ሊባኖሶችህን ይቆርጣሉ፤

ለእሳትም ይማግዷቸዋል።+

8 “‘ብዙ ብሔራትም በዚህች ከተማ በኩል ያልፋሉ፤ እርስ በርሳቸውም “ይሖዋ በዚህች ታላቅ ከተማ ላይ ይህን ያደረገው ለምንድን ነው?” ይባባላሉ።+ 9 እነሱም እንዲህ ብለው ይመልሳሉ፦ “የአምላካቸውን የይሖዋን ቃል ኪዳን ትተው ለሌሎች አማልክት ስለሰገዱና እነሱን ስላገለገሉ ነው።”’+

10 ለሞተው ሰው አታልቅሱ፤

ደግሞም አትዘኑለት።

ይልቁንም በግዞት ለተወሰደው አምርራችሁ አልቅሱ፤

ከእንግዲህ የትውልድ አገሩን ለማየት አይመለስምና።

11 “በአባቱ በኢዮስያስ ፋንታ ስለነገሠው፣ ከዚህም ቦታ ስለሄደው ስለ ይሁዳ ንጉሥ ስለ ኢዮስያስ ልጅ+ ስለ ሻሉም*+ ይሖዋ እንዲህ ይላልና፦ ‘ከእንግዲህ ወደዚያ አይመለስም። 12 በግዞት በተወሰደበት በዚያው ስፍራ ይሞታል እንጂ ይህን ምድር ዳግመኛ አያይም።’+

13 ጽድቅን በሚጻረር መንገድ ቤቱን ለሚገነባ፣

ፍትሕን በማዛባት ደርብ ለሚሠራ፣

የወገኑን ጉልበት እንዲሁ ለሚበዘብዝና

ደሞዙን ለማይከፍለው ወዮለት፤+

14 ‘ለራሴ ሰፊ ቤትና

የተንጣለለ ደርብ እገነባለሁ።

መስኮቶች እንዲኖረው አደርጋለሁ፤

በአርዘ ሊባኖስም እለብጠዋለሁ፤ ቀይ ቀለምም እቀባዋለሁ’ ለሚል ወዮለት!

15 በአርዘ ሊባኖስ እንጨት ከሌሎች ስለምትበልጥ በንግሥና የምትቀጥል ይመስልሃል?

አባትህም ቢሆን ይበላና ይጠጣ ነበር፤

ሆኖም ለፍትሕና ለጽድቅ ቆሟል፤+

እንዲህ በማድረጉም ተሳክቶለት ነበር።

16 ለተጎሳቆለው ሰውና ለድሃው ተሟግቷል፤

ስለዚህ መልካም ሆኖለት ነበር።

‘እኔን ማወቅ ማለት ይህ አይደለም?’ ይላል ይሖዋ።

17 ‘አንተ ግን ዓይንህና ልብህ ያረፈው አላግባብ በምታገኘው ጥቅም፣

ንጹሕ ደም በማፍሰስ

እንዲሁም በማጭበርበርና በቅሚያ ላይ ብቻ ነው።’

18 “ስለዚህ ይሖዋ ስለ ይሁዳ ንጉሥ ስለ ኢዮስያስ ልጅ ስለ ኢዮዓቄም+ እንዲህ ይላል፦

‘“ወይኔ ወንድሜን! ወይኔ እህቴን!”

ብለው አያለቅሱለትም።

“ወይኔ ጌታዬን! ክብሩ ሁሉ እንዲህ ይጥፋ!”

ብለው አያለቅሱለትም።

19 አህያ እንደሚቀበረው ይቀበራል፤+

ከኢየሩሳሌም በሮች ውጭ

ጎትተው ይጥሉታል።’+

20 ወደ ሊባኖስ ወጥተሽ ጩኺ፤

በባሳን ድምፅሽን አሰሚ፤

በአባሪም+ ሆነሽ ጩኺ፤

አጥብቀው የሚወዱሽ ሁሉ ደቀዋልና።+

21 ተማምነሽ በተቀመጥሽበት ጊዜ አነጋገርኩሽ።

አንቺ ግን ‘አልታዘዝም’ አልሽ።+

ከልጅነትሽ ጀምሮ ይህን ጎዳና ተከተልሽ፤

ቃሌን አልታዘዝሽምና።+

22 ነፋስ እረኞችሽን በሙሉ ይነዳቸዋል፤+

አጥብቀው የሚወዱሽም በግዞት ይወሰዳሉ።

በዚያን ጊዜ ከሚደርስብሽ ጥፋት ሁሉ የተነሳ ታፍሪያለሽ፤ ውርደትም ትከናነቢያለሽ።

23 አንቺ በሊባኖስ የምትኖሪ፣+

በአርዘ ሊባኖሶች መካከል ተደላድለሽ የተቀመጥሽ፣+

ጣር ሲይዝሽ፣

አዎ ልትወልድ እንደተቃረበች ሴት ጭንቅ* ሲይዝሽ ምንኛ ታቃስቺ ይሆን!”+

24 “‘በሕያውነቴ እምላለሁ’ ይላል ይሖዋ፣ ‘አንተ የይሁዳ ንጉሥ፣ የኢዮዓቄም+ ልጅ፣ ኮንያሁ*+ በቀኝ እጄ እንዳለ የማኅተም ቀለበት ብትሆን እንኳ ከዚያ አውጥቼ እጥልሃለሁ! 25 ሕይወትህን ለማጥፋት በሚሹ* ሰዎች እጅ፣ በምትፈራቸው ሰዎች እጅ፣ በባቢሎን ንጉሥ በናቡከደነጾር* እጅና በከለዳውያን እጅ አሳልፌ እሰጥሃለሁ።+ 26 አንተንና የወለደችህን እናትህን ወዳልተወለዳችሁበት፣ ወደ ሌላ አገር እወረውራችኋለሁ፤ በዚያም ትሞታላችሁ። 27 ወደሚናፍቋትም ምድር* ፈጽሞ አይመለሱም።+

28 ኮንያሁ የተባለው ይህ ሰው የተናቀና የተሰበረ ገንቦ፣

ማንም የማይፈልገው የሸክላ ዕቃ ነው?

እሱም ሆነ ዘሮቹ ወደማያውቋት ምድር የተወረወሩትና

የተጣሉት ለምንድን ነው?’+

29 ምድር፣* ምድር፣ አንቺ ምድር ሆይ፣ የይሖዋን ቃል ስሚ።

30 ይሖዋ እንዲህ ይላል፦

‘ይህን ሰው፣ ልጅ እንደሌለውና

በሕይወት ዘመኑ* ሁሉ ምንም እንደማይሳካለት አድርጋችሁ መዝግቡት፤

ከዘሮቹ መካከል አንዱም እንኳ አይሳካለትምና፤

በዳዊት ዙፋን ላይ አይቀመጥም እንዲሁም ይሁዳን ዳግመኛ አይገዛም።’”+

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ