2 ዜና መዋዕል 28:19, 20 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 19 ይሖዋ በእስራኤል ንጉሥ በአካዝ የተነሳ ይሁዳን አዋረደ፤ ምክንያቱም አካዝ የይሁዳን ሰዎች መረን ለቆ ነበር፤ ይህም ንጉሡ ለይሖዋ የነበረውን ታማኝነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያጓድል አደረገው። 20 በመጨረሻም የአሦር ንጉሥ ቴልጌልቴልፌልሶር+ እሱን ከመርዳት ይልቅ በእሱ ላይ ዘምቶ አስጨነቀው።+ ኢሳይያስ 7:17 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 17 ይሖዋ፣ ኤፍሬም ከይሁዳ ከተለየበት+ ጊዜ ጀምሮ ታይቶ የማይታወቅ ዘመን በአንተ፣ በሕዝብህና በአባትህ ቤት ላይ ያመጣል፤ የአሦርን ንጉሥ ያመጣልና።+ ኢሳይያስ 7:20 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 20 “በዚያም ቀን ይሖዋ በወንዙ* አካባቢ ከሚገኘው ቦታ በተከራየው ምላጭ ይኸውም በአሦር ንጉሥ+ አማካኝነት ራሱንና የእግሩን ፀጉር ይላጨዋል፤ ጢሙንም ሙልጭ አድርጎ ያስወግደዋል። ኢሳይያስ 10:28-32 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 28 በአያት+ ላይ መጥቷል፤ሚግሮንን አቋርጦ አልፏል፤በሚክማሽ+ ጓዙን ያስቀምጣል። 29 መልካውን* ተሻግረዋል፤በጌባ+ ያድራሉ፤ራማ ራደች፤ የሳኦል ከተማ ጊብዓ+ ሸሽታለች።+ 30 የጋሊም ሴት ልጅ ሆይ፣ እሪታሽን አቅልጪው! ላይሻ ሆይ፣ አዳምጪ! ምስኪኗ አናቶት+ ሆይ፣ ጩኺ! 31 ማድመና ሸሽታለች። የጌቢም ነዋሪዎች መሸሸጊያ ፈለጉ። 32 በዚሁ ቀን በኖብ+ ያርፋል። በጽዮን ሴት ልጅ ተራራ፣በኢየሩሳሌም ኮረብታ ላይ እጁን በዛቻ ያወዛውዛል።
19 ይሖዋ በእስራኤል ንጉሥ በአካዝ የተነሳ ይሁዳን አዋረደ፤ ምክንያቱም አካዝ የይሁዳን ሰዎች መረን ለቆ ነበር፤ ይህም ንጉሡ ለይሖዋ የነበረውን ታማኝነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያጓድል አደረገው። 20 በመጨረሻም የአሦር ንጉሥ ቴልጌልቴልፌልሶር+ እሱን ከመርዳት ይልቅ በእሱ ላይ ዘምቶ አስጨነቀው።+
20 “በዚያም ቀን ይሖዋ በወንዙ* አካባቢ ከሚገኘው ቦታ በተከራየው ምላጭ ይኸውም በአሦር ንጉሥ+ አማካኝነት ራሱንና የእግሩን ፀጉር ይላጨዋል፤ ጢሙንም ሙልጭ አድርጎ ያስወግደዋል።
28 በአያት+ ላይ መጥቷል፤ሚግሮንን አቋርጦ አልፏል፤በሚክማሽ+ ጓዙን ያስቀምጣል። 29 መልካውን* ተሻግረዋል፤በጌባ+ ያድራሉ፤ራማ ራደች፤ የሳኦል ከተማ ጊብዓ+ ሸሽታለች።+ 30 የጋሊም ሴት ልጅ ሆይ፣ እሪታሽን አቅልጪው! ላይሻ ሆይ፣ አዳምጪ! ምስኪኗ አናቶት+ ሆይ፣ ጩኺ! 31 ማድመና ሸሽታለች። የጌቢም ነዋሪዎች መሸሸጊያ ፈለጉ። 32 በዚሁ ቀን በኖብ+ ያርፋል። በጽዮን ሴት ልጅ ተራራ፣በኢየሩሳሌም ኮረብታ ላይ እጁን በዛቻ ያወዛውዛል።