የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • 2 ነገሥት 18:13
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 13 ንጉሥ ሕዝቅያስ በነገሠ በ14ኛው ዓመት የአሦር ንጉሥ ሰናክሬም+ በተመሸጉት የይሁዳ ከተሞች ሁሉ ላይ ዘምቶ ያዛቸው።+

  • 2 ዜና መዋዕል 32:1
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 32 እነዚህ ነገሮች ከተከናወኑና ሕዝቅያስ በታማኝነት ሲመላለስ+ ከቆየ በኋላ የአሦር ንጉሥ ሰናክሬም መጥቶ ይሁዳን ወረረ። ቅጥራቸውን አፍርሶ ለመያዝ ስላሰበ የተመሸጉትን ከተሞች ከበበ።+

  • ኢሳይያስ 8:7, 8
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    •  7 እነሆ፣ ይሖዋ ብርቱ የሆኑትንና ከፍተኛ መጠን ያላቸውን የወንዙን* ውኃዎች ይኸውም

      የአሦርን ንጉሥና+ ክብሩን ሁሉ

      በእነሱ ላይ ያመጣባቸዋል።

      እሱም የውኃ መውረጃዎቹን ሁሉ ሞልቶ ይፈስሳል፤

      ዳርቻዎቹንም ሁሉ ያጥለቀልቃል፤

       8 ይሁዳንም ጠራርጎ ይሄዳል።

      አካባቢውን እያጥለቀለቀ በማለፍ እስከ አንገት ይደርሳል፤+

      አማኑኤል*+ ሆይ፣ የተዘረጉት ክንፎቹ

      ምድርህን ከዳር እስከ ዳር ይሸፍናሉ!”

  • ኢሳይያስ 10:28-32
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 28 በአያት+ ላይ መጥቷል፤

      ሚግሮንን አቋርጦ አልፏል፤

      በሚክማሽ+ ጓዙን ያስቀምጣል።

      29 መልካውን* ተሻግረዋል፤

      በጌባ+ ያድራሉ፤

      ራማ ራደች፤ የሳኦል ከተማ ጊብዓ+ ሸሽታለች።+

      30 የጋሊም ሴት ልጅ ሆይ፣ እሪታሽን አቅልጪው!

      ላይሻ ሆይ፣ አዳምጪ!

      ምስኪኗ አናቶት+ ሆይ፣ ጩኺ!

      31 ማድመና ሸሽታለች።

      የጌቢም ነዋሪዎች መሸሸጊያ ፈለጉ።

      32 በዚሁ ቀን በኖብ+ ያርፋል።

      በጽዮን ሴት ልጅ ተራራ፣

      በኢየሩሳሌም ኮረብታ ላይ እጁን በዛቻ ያወዛውዛል።

  • ኢሳይያስ 33:8
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    •  8 አውራ ጎዳናዎቹ ጭር ብለዋል፤

      በመንገድ ላይ የሚጓዝ ሰው የለም።

      እሱ* ቃል ኪዳኑን አፍርሷል፤

      ከተሞቹን ንቋል፤

      ሟች ለሆነው ሰው ደንታ የለውም።+

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ