8 ከሰሜን ምድር መልሼ አመጣቸዋለሁ።+
ከምድር ዳርቻዎች እሰበስባቸዋለሁ።+
በመካከላቸው ዓይነ ስውርና አንካሳ፣+
ነፍሰ ጡርና ልትወልድ የተቃረበች ሴት በአንድነት ይገኛሉ።
ታላቅ ጉባኤ ሆነው ወደዚህ ይመለሳሉ።+
9 እያለቀሱ ይመጣሉ።+
ሞገስ ለማግኘት ሲለምኑ እየመራሁ አመጣቸዋለሁ።
ወደ ውኃ ጅረቶች እመራቸዋለሁ፤+
በማይሰናከሉበት ደልዳላ መንገድ እወስዳቸዋለሁ።
እኔ ለእስራኤል አባት ነኝና፤ ኤፍሬምም የበኩር ልጄ ነው።”+