የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ኢሳይያስ 40:20
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 20 አንድ ሰው መዋጮ አድርጎ ለመስጠት

      የማይበሰብስ ዛፍ ይመርጣል።+

      የማይወድቅ ምስል ቀርጾ እንዲያዘጋጅለት

      በእጅ ጥበብ ሥራ የተካነ ባለሙያ ይፈልጋል።+

  • ኢሳይያስ 44:14, 15
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 14 አርዘ ሊባኖስ የሚቆርጥ ሰው አለ።

      እሱም አንድ የዛፍ ዝርያ ይኸውም የባሉጥ ዛፍ ይመርጣል፤

      እስኪጠነክርለት ድረስ በጫካው ውስጥ ባሉት ዛፎች መካከል ይተወዋል።+

      የላውሮ ዛፍ ይተክላል፤ ዝናብም ያሳድገዋል።

      15 ከዚያም ሰው ለማገዶ ይጠቀምበታል።

      የተወሰነውን እንጨት ወስዶ በማንደድ እሳት ይሞቃል፤

      እሳት አያይዞም ዳቦ ይጋግራል።

      ይሁንና አምላክ ሠርቶም ያመልከዋል።

      የተቀረጸ ምስል ሠርቶበት በፊቱ ይደፋል።+

  • ኢሳይያስ 45:20
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 20 ተሰብስባችሁ ኑ።

      እናንተ ከብሔራት ያመለጣችሁ፣ በአንድነት ቅረቡ።+

      የተቀረጹ ምስሎቻቸውን ተሸክመው የሚዞሩም ሆኑ

      ሊያድናቸው ወደማይችል አምላክ የሚጸልዩ+ ምንም እውቀት የላቸውም።

  • ዕንባቆም 2:18
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 18 የተቀረጸ ምስል፣

      ሠሪው የቀረጸው ከሆነ ምን ጥቅም አለው?

      ሠሪው እምነት ቢጥልበትም እንኳ

      ከብረት የተሠራ ሐውልትና* ሐሰትን የሚናገር አስተማሪ ምን ፋይዳ አለው?

      መናገር የማይችሉ ከንቱ አማልክት መሥራት ምን እርባና አለው?+

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ