ኅዳር 5 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
ኅዳር 5 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 48 እና ጸሎት
□ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
w09 2/15 ገጽ 11-12 ከአን. 8-14 (30 ደቂቃ)
□ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ ኢዩኤል 1-3 (10 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ ኢዩኤል 2:17-27 (4 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ ምሳሌ 22:3 ላይ የሚገኘውን ምክር ተግባራዊ ልናደርግ የምንችልባቸው አንዳንድ መንገዶች የትኞቹ ናቸው? (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ ለይሖዋ ድርጅት አክብሮት እንዳለን ማሳየት የምንችለው እንዴት ነው?—rs ገጽ 284 ከአን. 1-5 (5 ደቂቃ)
□ የአገልግሎት ስብሰባ፦
10 ደቂቃ፦ ምሥራቹን የሚያውጁት ሴቶች ታላቅ ሠራዊት ናቸው። (መዝ. 68:11 የ1980 ትርጉም) በ2012 የዓመት መጽሐፍ (እንግሊዝኛ) ከገጽ 117 አንቀጽ 2 እስከ ገጽ 118 አንቀጽ 2 እንዲሁም ከገጽ 130 አንቀጽ 1 እስከ ገጽ 131 አንቀጽ 2 ላይ ተመሥርቶ በውይይት የሚቀርብ። ምን ትምህርት እንዳገኙ አድማጮችን ጠይቅ።
10 ደቂቃ፦ ለጉባኤው እንደሚያስፈልግ ተጠቀሙበት።
10 ደቂቃ፦ በኅዳር ወር መጽሔቶችን ለማበርከት የሚረዱ ሐሳቦች። በውይይት የሚቀርብ። መጽሔቶቹ በክልላችሁ ውስጥ ያሉ ሰዎችን ትኩረት ሊስቡ የሚችሉበትን ምክንያት ከ30 እስከ 60 ሴኮንድ ባለው ጊዜ ውስጥ ተናገር። ከዚያም በመጠበቂያ ግንብ መጽሔት የሽፋን ርዕስ ዙሪያ የሰዎችን የማወቅ ፍላጎት ለመቀስቀስ ምን ጥያቄ ማንሳት እንዲሁም የትኞቹን ጥቅሶች ማንበብ እንዳሰቡ አድማጮችን ጠይቅ። በንቁ! መጽሔት የሽፋን ርዕስ ዙሪያም ተመሳሳይ ጥያቄዎችን አቅርብ፤ ጊዜ ካለህ ከመጠበቂያ ግንብ ወይም ከንቁ! መጽሔት አንድ ተጨማሪ ርዕስ ማከል ትችላለህ። እያንዳንዱን መጽሔት እንዴት ማበርከት እንደሚቻል የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ።
መዝሙር 15 እና ጸሎት