የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 10/00 ገጽ 10
  • አዲስ የወረዳ ስብሰባ ፕሮግራም

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • አዲስ የወረዳ ስብሰባ ፕሮግራም
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2000
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • አዲስ የወረዳ ስብሰባ ፕሮግራም
    የመንግሥት አገልግሎታችን—1998
  • መንፈሳዊነታችንን እንድንጠብቅ የሚረዳን የወረዳ ስብሰባ
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2009
  • አዲስ የወረዳ ስብሰባ ፕሮግራም
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2001
  • ለክርስቲያን አገልጋዮች የተደረገ ዝግጅት
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2010
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—2000
km 10/00 ገጽ 10

አዲስ የወረዳ ስብሰባ ፕሮግራም

ይሖዋ ልናፈቅረውና ለእርሱ ብቻ የተወሰነ አምልኮ ልናቀርብለት የሚገባው አምላክ እንደሆነ እናውቃለን። ይሁን እንጂ ከአምላክ ጋር የመሠረትነውን የጠበቀ ወዳጅነት እንድናላላ ዓለም ሊያ​ታልለን ይፈልጋል። (ዮሐ. 17:​14) ለይሖዋ ያለንን ፍቅር ለማጠንከርና በመንፈሳዊነታችን ላይ አደጋ የሚጥሉትን የዓለም ነገሮች እንድናሸንፍ ብርታት ለመስጠት የ2001 የአገልግሎት ዓመት አዲስ የወረዳ ስብሰባ ፕሮግራም “አምላክን እንጂ በዓለም ያሉትን ነገሮች አትውደዱ” በሚል ጭብጥ ተዘጋጅቷል።​—⁠1 ዮሐ. 2:​15-17

ለይሖዋ ያለን ጥልቅ ፍቅር ስለ እርሱ እንድንመሠክር ይገፋፋናል። ያም ሆኖ ለብዙዎቹ የአምላክ ሕዝቦች የመስክ አገልግሎት እንዲህ ቀላል አይደለም። “ለአምላክ ያለን ፍቅር እንድናገለግል ይገፋፋናል” የሚለው ንግግር ብዙዎች በዚህ ሥራ ሙሉ ተሳትፎ ለማድረግ ዓይናፋርነትንና ሌሎች መሰናክሎችን እንዴት እንዳሸነፉ እንማራለን።

እያዘቀጠ የመጣው የዓለም የሥነ ምግባር ደረጃ ተጽዕኖ የሚያሳድርብን እንዴት ነው? በአንድ ወቅት እንደ ነውር ይታዩ የነበሩ ሁኔታዎች አሁን የተለመዱ ሆነዋል። “ይሖዋን የሚወዱ ክፋትን ይጠላሉ” የሚለው ንግግርና “በዓለም ላሉ ነገሮች ያለን አመለካከት ምንድን ነው?” በሚል ርዕስ የሚቀርበው ሲምፖዚየም መጥፎ ምኞቶችን እምቢ ለማለት ያደረግነውን ቁርጥ ውሳኔ ያጠናክርልናል።

ፕሮግራሙ የቲኦክራሲያዊ አገልግሎት ትምህርት ቤት እና የአገልግሎት ስብሰባ ናሙናዎችን የሚያካትት ሲሆን የሳምንቱ የመጠበቂያ ግንብ ጥናት በክለሳ ይቀርባል። “ፍቅርና እምነት ዓለምን የሚያሸንፉት እንዴት ነው?” በሚል ርዕስ የሚቀርበው የሕዝብ ንግግር ዓለማዊ ተጽዕኖዎችን በመቋቋም ረገድ የኢየሱስን ምሳሌ እንድንኮርጅ ማበረታቻ ይሰጠናል። (ዮሐ. 16:​33) ጥናቶችህ በስብሰባው ላይ እንዲገኙ መጋበዝ አትርሳ። አስፈላጊ የሆኑ ዝግጅቶችን ማድረግ እንዲቻል መጠመቅ የሚፈልጉ ሁሉ በተቻለ መጠን ቀደም ብለው ለሰብሳቢ የበላይ ተመልካቹ መንገር ይገባቸዋል።

ይሖዋ የሚያመጣውን ታላቅ በረከት ለማጣጣም ፍቅራችን የት ቦታ ላይ ማረፍ እንዳለበት ትኩረት እንድናደርግ ይህ የወረዳ ስብሰባ ይረዳናል። የትኛውም የስብሰባው ክፍል እንዳያመልጥህ!

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ