የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • መዝሙር 14:1-7
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 14 ሞኝ* ሰው በልቡ

      “ይሖዋ የለም” ይላል።+

      ሥራቸው ብልሹ ነው፤ ተግባራቸውም አስጸያፊ ነው፤

      መልካም የሚሠራ ማንም የለም።+

       2 ሆኖም ጥልቅ ማስተዋል ያለውና ይሖዋን የሚፈልግ ሰው ይኖር እንደሆነ ለማየት፣

      ይሖዋ ከሰማይ ሆኖ ወደ ሰው ልጆች ይመለከታል።+

       3 ሁሉም መንገድ ስተዋል፤+

      ሁሉም ብልሹ ናቸው።

      መልካም የሚሠራ ማንም የለም፤

      አንድ እንኳ የለም።

       4 ከክፉ አድራጊዎቹ መካከል አንዳቸውም አያስተውሉም?

      ምግብ እንደሚበሉ ሕዝቤን ይውጣሉ።

      ይሖዋን አይጠሩም።

       5 ይሁንና በታላቅ ሽብር ይዋጣሉ፤+

      ይሖዋ ከጻድቅ ትውልድ ጋር ነውና።

       6 እናንተ ክፉ አድራጊዎች የችግረኛውን ሰው ዕቅድ ለማጨናገፍ ትሞክራላችሁ፤

      ይሖዋ ግን መጠጊያው ነው።+

       7 የእስራኤል መዳን ምነው ከጽዮን በመጣ!+

      ይሖዋ የተማረከውን ሕዝቡን በሚመልስበት ጊዜ፣

      ያዕቆብ ደስ ይበለው፤ እስራኤል ሐሴት ያድርግ።

  • ሮም 3:10
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 10 ይህም እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈው ነው፦ “ጻድቅ ሰው የለም፤ አንድም እንኳ የለም፤+

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ