የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 2/12 ገጽ 4
  • የአቀራረብ ናሙናዎች

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የአቀራረብ ናሙናዎች
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2012
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • መጽሔቶችን ለማበርከት ምን ማለት ይቻላል?
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2011
  • የናሙና አቀራረቦች
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2011
  • የአቀራረብ ናሙናዎች
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2012
  • የአቀራረብ ናሙናዎች
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2011
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—2012
km 2/12 ገጽ 4

የአቀራረብ ናሙናዎች

በወሩ የመጀመሪያ ቅዳሜ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶችን ማስጀመር

“ብዙ ሰዎች የኢየሱስን ልደት ያከብራሉ፤ ይሁንና የኢየሱስንስ ሞት ማክበር አስፈላጊ ይመስልዎታል?” ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው። ከዚያም የመጋቢት 1⁠ን መጠበቂያ ግንብ ስጠውና ገጽ 16 ላይ በሚገኘው በመጀመሪያው ንዑስ ርዕስ ሥር ያለውን ሐሳብ አብራችሁ ተመልከቱ፤ በተጨማሪም እዚያ ላይ ከተጠቀሱት ጥቅሶች መካከል ቢያንስ አንዱን አብራችሁ አንብቡ። ከዚያም በቀጣዩ ጥያቄ ላይ ለመወያየት ቀጠሮ ያዝ።

መጋቢት 1 መጠበቂያ ግንብ

“የተለያዩ እምነቶችና ልማዶች ያሏቸው በርካታ ቤተ ክርስቲያኖችና ሃይማኖታዊ ቡድኖች አሉ። ሆኖም “ክርስቲያን” ነን የሚሉ ሁሉ በእርግጥ ክርስቲያኖች ይመስልዎታል? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] ኢየሱስ በ⁠ዮሐንስ 13:34, 35 ላይ እውነተኛ ክርስቲያኖችን ለይቶ የሚያሳውቅ አንድ ምልክት ተናግሯል። [ጥቅሱን አንብብ።] ይህ መጽሔት እውነተኛ ክርስቲያኖችን ለይተን ለማወቅ የሚያስችሉንን ኢየሱስ የተናገራቸውን አምስት ነጥቦች ያብራራል።”

መጋቢት ንቁ!

“በሰዎች ዘንድ እየተለመደ ስለመጣ አንድ አሳሳቢ ችግር ከጎረቤቶችዎ ጋር እየተወያየን ነበር። በዛሬው ጊዜ ሰዎች ቁጣቸውን መቆጣጠር እያቃታቸውና ከበፊቱ የበለጠ ግልፍተኞች እየሆኑ የመጡ ይመስላል። ይህ የሆነበት ምክንያት ምን ይመስልዎታል? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] መጽሐፍ ቅዱስ በ⁠መዝሙር 37:8 ላይ ስለ ቁጣ ምን እንደሚል ልብ ይበሉ። [ጥቅሱን አንብብ።] ይህ መጽሔት በዛሬው ጊዜ ሰዎች ቁጡ የሆኑበትን ምክንያትና ቁጣችንን መቆጣጠር የምንችልባቸውን መንገዶች ይጠቁማል።”

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ