የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘዳግም 30:1-3
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 30 “ይህ ቃል ሁሉ ይኸውም በፊትህ ያስቀመጥኩት በረከትና እርግማን+ በአንተ ላይ በሚመጣበትና አምላክህ ይሖዋ በመካከላቸው እንድትበተን ባደረገህ ብሔራት ምድር+ ሆነህ ይህን ቃል ሁሉ በምታስታውስበት* ጊዜ+ 2 እንዲሁም አንተም ሆንክ ልጆችህ እኔ ዛሬ በማዝህ ትእዛዝ ሁሉ መሠረት በሙሉ ልባችሁና በሙሉ ነፍሳችሁ*+ ወደ አምላካችሁ ወደ ይሖዋ በምትመለሱበትና ቃሉን በምትሰሙበት ጊዜ+ 3 አምላክህ ይሖዋ ተማርከው የተወሰዱብህን ይመልስልሃል፤+ ምሕረትም ያሳይሃል፤+ እንዲሁም አምላክህ ይሖዋ በመካከላቸው እንድትበተን ካደረገህ ሕዝቦች ምድር ሁሉ መልሶ ይሰበስብሃል።+

  • ኢሳይያስ 11:16
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 16 እስራኤል ከግብፅ ምድር በወጣበት ጊዜ እንደሆነው ሁሉ፣

      ከሕዝቡ የተረፉት ቀሪዎችም+ ከአሦር የሚወጡበት ጎዳና+ ይኖራል።

  • ኢሳይያስ 43:6
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    •  6 ሰሜንን ‘ልቀቃቸው!’ እለዋለሁ፤+

      ደቡብንም እንዲህ እለዋለሁ፦ ‘አታግታቸው።

      ወንዶች ልጆቼን ከሩቅ፣ ሴቶች ልጆቼንም ከምድር ዳርቻ አምጣ፤+

  • ኢሳይያስ 60:4
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    •  4 ዓይንሽን አንስተሽ ዙሪያሽን ተመልከቺ!

      ሁሉም አንድ ላይ ተሰብስበዋል፤ ወደ አንቺም እየመጡ ነው።

      ከሩቅ ቦታ ወንዶች ልጆችሽ በመምጣት ላይ ናቸው፤+

      ሴቶች ልጆችሽም ታዝለው እየመጡ ነው።+

  • ኢሳይያስ 60:9
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    •  9 ደሴቶች እኔን ተስፋ ያደርጋሉና፤+

      የተርሴስ መርከቦችም ከሩቅ ወንዶች ልጆችሽን

      ከነብራቸውና ከነወርቃቸው

      ለአምላክሽ ለይሖዋ ስምና ለእስራኤል ቅዱስ ለማምጣት+

      ቀዳሚ ሆነው* ይወጣሉ፤

      እሱ ክብር* ያጎናጽፍሻልና።+

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ